Tuesday, April 29, 2014

ኦሮሚያ የኦሮሞዎች ናት – የኦሮሞ ተማሪዎች

April 28/2014

በአራት ዪኒቨርሲቲዎች የሚገኙ የኦሮሞ ተማሪዎች የአዲስ አበባ አዲሱን ማስተር ፓልን በመቃወም ተቃዉሞውውቸዉን አሰሙ።
በዉጭ አገር የሚገኘውና በቅርቡ የተቋቋመው የኦሮሞ ሜዲያ ንቴዎርክ ማስተር ፓልኑን በመቃወም ከፍተኛ ቅስቀሳ እያደረገ የነበረና የሚገኝ ሲሆን፣ በዶር መራራ ጉዳናን የሚመራዉ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስን ጨመሮ በርካታ የኦሮሞ ድርጅቶች በርካታ የኦሮሞ ድርጅቶች ፕላኑን አዉግዘዋል።
የኦሮሞ ተማሪዎች ም በአምቦ፣ በወለጋ፣ በጂማና በሃረማያ ሰላማዊ በሆነመንገድ ተቃዉሟቸውን ለማሰማት የሞከሩ ሲሆን፣ በአጸፋው የፌዴራል ፖሊስ ከፍተኛ ደብደባ በተማሪዎች ላይ እንዳደረሰ ለማወቅ ችለናል።
በወላጋ ፖሊስ ጥይት የተኮሰ ሲኦሆን በርካቶች እንደቆሰሉ የተቀረኡትን በአካባቢዉ ወዳለ ጫካ እንደትበታተኑ ለማወቅ ተችሏል። በጂማ 11 በአምቦ ደግሞ 15 ተማሪዎች ታስረዋል።
ተማሪዎቹ «ቡራዩ አይሸጥም፣ ሱሉልታ አይሸጠም፣ ለገጣፎ አይሸጥም፣ ኦሮሚያ ለኦሮሞዎች ብቻ ! ፊንፊኔ የኦሮሚያ ናት..» የመሳሰሉ መፈክሮችን ሲያሰሙም ነበር።
በኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አዲስ አበባ የኦሮሚያ አካል እንደሆነች በግልጽ የተቀመጠ ሲሆን፣ ኦሮሚያ ከአዲስ አበባ ማግኘት ያለባትን ጥቅም ማግኘት እንደሚኖርባትም ይደነግጋል። የኢትዮዮጵያ ግዛት ባለቤት የኢትዮጵያ ሕዝብ ሳይሆን ብሄረ ብሄረሰቦች እንደሆነ የሚደነግገው ሕገ መንግስቱ፣ ብሄር ብሄረሰቦች ራሳቸው በራስ የማስተዳደር መብት ያዉም እስከመገንጠል እንደሚፈቅድም ይታወቃል።
አገሪቷ በቋንቋ ላይ የተመሰረተ ፌዴራል አወቃቀር እንዲኖራት የተደረገ ሲሆን፣ ይሄም አወቃቀር ያል ሕዝብ ፍቃደ በኦነግ፣ በሕወሃት እና በሻቢያ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እንደሆነ ይታወቃል።
የኦሮሚያ ሕግ መንግስት የኦሮሚያ ባለቤት ኦሮሞ ብቻ እንደሆነ በአንቀጽ ስምንት ባስቀመጠዉ መሰረት፣ ኦሮሞ ያልሆኑ ኢትዮጵያዊያን በኦሮሚያ ዉስጥ እንደ እንግዳ እንደሚታዩም የሚገልጹ በርካታ ክስተቶች አሉ።
በኦሮሞ ተማሪዎች ሲባሉ የነበሩት «ኦሮሚያ የኦሮሞውች ናት። አዲስ አበባ የኦሮሚያ ናት» የሚሉት መፈክሮች፣ አገዛዙ ራሱ በሰነድና በወረቀት የሚቀበለውና የሚስማማበት እንደመሆኑ፣ ተማሪዎች ሰላማዊ በህነ መንገድ በኦሮሚያ ሕግ መንግስት ዬትቀመጠዉን በመድገማቸው መደብደባቸው ፣ አሳፋሪ እና አዛዝኝ እንደሆነም ብዙዎች እየተናገሩ ነው።
ዜጎች በኢሕአደግ ባለስልጣናት ከቅያቸው የሚፈናቀሉት በሁሉም ክልሎች እንደሆነ የገለጹት ያነጋገርናቸው አንድ የፖለቲክ ተንታኝ ፣ በልማት ስም በኦሮሞዎችም ሆነ በማንም ኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርስን ግፍ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ መቃወም እንዳለበት ይናግራሉ። አዲስ አበባን በተመለከተ « አዲስ አበባ ማደጓ አይቀርም። እድገቷ ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ይፈጸም መባል ነው እንጂ ያለበት፣ የኦሮሚያ ሬፑብሊክ ወደፊት ለመፍጠር ከሚኖር ፍላጎት የተነሳ የኦሮሚያ ክልል ለምን አነሰች የሚል ጠባብ መከራከሪያ የትም አያደርስም።» ሲሉ ተማሪዎቹም ሆነ በዉጭ ያሉ የኦሮሞ ብሄረተኞች ያለዉን ተጨባጭ እዉነታ እንዲገነዘቡም ይመክራሉ።
oromo1
oromo2
oromo3

No comments: