Saturday, October 31, 2015

አይኔ አያየ እዚህ ዉስጥ አልገባም – መሠረት ሙሌ (ኤፍሬም ማዴቦ ከአርበኞች መንደር)

October 31, 2015
ኤፍሬም ማዴቦ ከአርበኞች መንደር
መብራቱን አጥፍቼዉ አልጋዬ ላይ የወጣሁት በግዜ ነዉ። አለወትሮዬ እንቅልፍ የሚባል ነገር በአይኔ አልዞር ብሎኝ ከጨለማዉ ጋር ፊት ለፊት ተፋጥጠናል። የነፋስ ሸዉታ እንኳን የማይሰማበት ደረቅ ሌሊት ነዉ። ጨላማዉ አይን ይበሳል። እቤቱ ዉስጥ ያለዉ ሰዉ ሁሉ ተኝቷል። ቀኑን በሠላም ላዋለኝ አምላክ ምስጋና ሰጥቼ ሌሊቱንም አደራ ብዬዉ ፀሎቴን ጨረስኩ። ያ ምቀኛ እንቅልፍ ግን አሁንም እንደከዳኝ ነዉ። ትንሿ አልጋዬ ላይ ግራ ቀኝ እያልኩ ተገለባበጥኩ። እንቅልፍ ተጎትቶ የሚመጣ ይመስል አሁንም አሁንም ላይ ታች እያልኩ አልጋዉ ላይ እራሴን ጎተትኩት . . . እንኳን እንቅልፍ ሊወስደኝ ጭራሽ አይኖቼ መርገብገባቸዉን ያቆሙ ይመስል ቀጥ ብለዉ ቀሩ። ከተጋደምኩበት ብድግ ብዬ መብራቱን አበራሁና ለመንገድ ከያዝኳቸዉ ሁለት መጻህፍት አንዱን አዉጥቼ ማንበብ ጀመርኩ። እኔ ላንብበዉ ወይ መጽሀፉ ያንብበኝ አላዉቅም። ጧት ስነሳ ግን “The Architecture of Democracy” የሚል መጽሐፍ ደረቴ ላይ ተለጥፎ ነበር። ሰዐቴን ሳየዉ ከሌሊቱ ስምንት ሰዐት ተኩል ይላል። ከአልጋዬ ላይ ዘልዬ ወረድኩና ሰዉነቴን ታጥቤ ልብሴን ከለበስኩ በኋላ መኪናዉ ዉስጥ ገብቼ “I’m ready” አልኩ። የመኪናችን መብራት ጨለማዉን እየገላለጠዉ የአስመራ ከረንን መንገድ ተያያዝነዉ። መኪናዉ ዉስጥ ከገባሁ በኋላ እንደገና አፌን የከፈትኩት ባሬንቱ ደርሰን ቁርስ ሳዝ ነዉ። ባሬንቱ በግዜ መድረሳችን ደስ ቢለኝም የቀረን መንገድ ርዝመት ታየኝና ቁርስ መብላቴን ትቼ . . . በሰዐት ይህን ያክል ብንጓዝ እያልኩ ዋናዉ ጉዳያችን ቦታ የምንደርስበትን ሰዐት ማስላት ጀመርኩ። የስሌቱ ዉጤት ከሦስት ሰዐት ሲበልጥብኝ ተናደድኩ። ቀሪዉ መንገድ ገና ሳልጀምረዉ ሰለቸኝ። በተፈጥሮዬ መንገድና መኃላ ሲረዝም አልወድም።Patriotic Ginbot7 fighters
ተሰነይ ስንደርስ መኪናዉ ዉስጥ የነበረዉ ሰዉ ሁሉ ቡና ካልጠጣሁ አለ። መኪናችንን አቁመን በቁማችን ቡናችንን ፉት አድርገን መንገዳችንን ተያያዝነዉ። እሁድ ጥቅምት 7 ቀን 2008 ዓም አርበኞች ግንቦት ሰባትን የፈጠሩት ሁለት ድርጅቶች ከተዋሃዱ በኋላ ለሁለተኛ ግዜ የሰለጠኑ ታጋይ አርበኞች የሚመረቁበት ቀን ነበር። ከዚህ ቀደም እንደዚህ አይነቱን የምርቃት ዜና የምሰማዉ በኢሳት ሬዲዮና ቴሌቭዥን ብቻ ስለነበር እቦታዉ ደርሼ የምረቃዉን ስነስርዐት ለማየት የነበረኝ ጉጉት እጅግ በጣም ከፍተኛ ነበር። የምሳ ሰዐት ከመድረሱ በፊት በቀኝ በኩል ዋናዉን መንገድ ለቅቀን ዉስጥ ዉስጡን ወደ ምርቃቱ ቦታ የሚወስደዉን ኮረኮንች መንገድ ተያያዝነዉ።
ግቢዉ ዉስጥ ያለዉ ጥድፊያና ግርግር አንድ ትልቅ ዝግጅት መኖሩን በግልጽ ይናገራል። የተለያየ ወታደራዊ ዩኒፎርም የለበሱና መሳሪያ የተሸከሙ አርበኞች ግቢዉን ሞልተዉታል። ያነገቱትን ጠመንጃ ስመለከት ቆራጥነታቸዉ ታየኝ። በቀጭኑ ተጎንጉኖ ማጅራታቸዉ ላይ የወደቀዉን ፀጉራቸዉን ሳይ ቴዎድሮስና ዮሐንስ ትዝ አሉኝ። ፈገግታ በፈገግታ የሆነዉን ፊታቸዉን ስመለከት ደግሞ የእናት አገሬ ኢትዮጵያ ትንሳኤ ደጃፍ ላይ መሆኑ ታየኝና የኔም ፊት እንደነሱ በፈገግታ ተሞላ። ተራ በተራ እየመጡ “ጋሼ አፍሬም” እንደኳን ደህና መጣህ ብለዉ ሲጠመጠሙብኝ በአንዱ ትከሻዬ ፍቅራቸዉ በሌላዉ ጀግንነታቸዉ ዘልቆ ሰዉነቴ ዉስጥ ገባ። ጥንካሬያቸዉ በጅማቴ ፍቅራቸዉ በደም ስሬ ዘለቀ። እኔነቴ ሲታደስና በአገሬ ላይ ያለኝ ተስፋ ሲለመልም ተሰማኝና ደስ አለኝ። አዎ ደስ አለኝ . . . እየመጣ የሚሄድ ግዜያዊ ደስታ ሳይሆን የዉስጥ አካላቴን የዳሰሰ ዘላቂ የመንፈስ ደስታ ተሰማኝ። በጣም ደስ የሚልና በአሁኖቹ ቋንቋ “የሚመች” ቀን ነበር። የዕለቱን ዝግጅት ለማየት መቸኮሌን ያወቁት እግሮቼ የምረቃዉ በዐል ወደሚከበርበት ዳስ- ፍትህ፤ ነጻነትና እኩልነት የናፈቀዉ ልቤ ደግሞ ወደ ወደፊቷ ኢትዮጵያ ይዘዉኝ ጭልጥ አሉ፡ . . . ለካስ የወደፊቷ ኢትዮጵያ ሩቅ አይደለችም።
“ማነዉ ሚለየዉ . . .ሚለየዉ፤ ይህም ትዉልድ ፍም እሳት ነዉ” የሚለዉን የጃሉድ ዘፈን በርቀት ሲሰማ በቀኑና በዘፈኑ መግጠም ተገረምኩ። “እዉነትም ይህ ትዉልድ ፍም እሳት ነዉ” እያልኩ በለሆሳስ ለራሴ እየነገርኩት ዳሱ ዉስጥ ገብቼ ቁጭ አልኩ። እርግጠኛ ነኝ ይህንን ጽሁፍ የሚያነብ ሰዉ ዳሱ ዉስጥ የነበረዉን ፍጹም ኢትዮጵያዊ የሆነ የጀግንነት፤ የቆራጥነት፤ የእልህና የመተማመን ልዩ ስሜት መረዳት የሚችለዉ እኔ በዚህ ባልተባ ብዕሬ ስገልጸዉ ሳይሆን እንዳዉ በደፈናዉ ዳሱ እራሱ ኢትዮጵያዊ ነበር ብዬ ባልፈዉ ነዉ።
አገራችን ኢትዮጵያ ከራሱ ምቾትና የተደላደለ ኑሮ ይልቅ የወገኖቹ መብትና ነጻነት የሚያንገበግበዉና እራሱን ለፍትህ፤ ለአንድነትና ለነጻነት ለመሰዋት ዝግጁ የሆነ የየዘመኑ ምርጥ ትዉልድ አላት። ይህንን የኛን ዘመን ምርጥ ትዉልድ ነዉ አርቲስት ጃሉድ “ይህም ትዉልድ ፍም እሳት ነዉ” ብሎ በጣፋጭ ዜማዉ ያወደሰዉ። እኔ ጥርጥርም የለኝ ይህ ትዉልድ አንድና ሁለት ብቻ ሳይሆን ለቁጥር የሚታክቱ ብዙ ፍም እሳቶች አሉት። ችግሩ የእሳት ነገር አዚህ ቤት ነደዳ እዚያም ቤት ነደደ ስራዉ ማቃጠል ነዉና አንዱን እሳት ከሌላዉ እሳት መለየት አስቸጋሪ ነዉ። እኔም ችግሬ እዚህ ላይ ነዉ። ፊት ለፊቴ ላይ ቁጭ ብለዉ ስለማያቸዉ ፍም እሳቶች (ጀግኖች) ላወራችሁ እየፈለኩ ምርጫዉ አዋጅ ሆነብኝ. . . የራሱ ጉዳይ ብዬ አንዱን ጀግና መረጥኩ። ይህንን ዛሬ የምተርክላችሁን ጀግና ስመርጥ ግን እንዳዉ በደፈና አልነበረም። ጉዳይ አለኝ . . . . ጉዳዩ አንዲህ ነዉ።
በዕለቱ በተመራቂ አርበኞች ተዘጋጅተዉ ከቀሩቡት የተለያዩ የኪነት ስራዎች ዉስጥ አንዱ የድራማ ዝግጅት ነበር። ሦስት የተለያዩ ድራማዎች መታየታቸዉ ትዝ ይለኛል። ዳሱ ዉስጥ የተሰበሰበዉን በብዙ መቶዎች የሚቆጠር ሰዉ ስሜት የኮረኮረዉና የእያንዳንዱን ሰዉ የልብ ትርታ ሰቅዞ የያዘዉ ግን በእዉነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተከወነዉ የመጨረሻዉ ድራማ ነበር። ድራማዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ በተለይ ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ የአርበኞች ግንቦት 7 አባላት ናችሁ እየተባለ በየቀኑ በህወሃት የደህንነት ሠራተኞች እጃቸዉ እየታሰረ በየወንዙና በየፈፋዉ በግፍ እየተገደሉ ስለሚጣሉ ኢትዮጵያዉያን የሚተርክ ድራማ ነበር።
ድራማዉ “ኮሜዲ” የሚባል ክፍል የለዉም። ተጀምሮ እስኪያልቅ “ትራጄዲ” ብቻ ነዉ። ያሳዝናል፤ ያስቆጣል፤ ያስቆጫል፤ያንገበግባል፤ አንጀት ያቆስላል፤ ልብ ያነድዳል . . . ወይ ነዶ ያሰኛል ። እኔማ እንኳን ትራጄዲ አይቼ በተፈጥሮዬ ሆደ ቡቡ ነኝና በደል ስመለከት ማዘን ልማዴ ሆኖ አምባዬ መፍሰስ የጀመረዉ ገና ድራማዉ ሲጀምር ነበር። በተለይ አናታቸዉ እየተደበደበ የሚቀበሩበትን ጉድጓድ በግድ እንዲቆፍሩ የተደረጉትን ሁለት ወጣት ወገኖቼን ሳይ ሆዴ ባባ፤ አንጀቴም ቆሰለ። ልቤ ዉሰጥ የነደደዉ እሳት ትንታጉ እየተንቦገቦገ ወጥቶ የዉጭ ሰዉነቴን ጭምር ለበለበዉ። ለወትሮዉ ነገር ማመዛዘን የሚቀድመዉ አዕምሮዬ በቀል በቀል አሰኘዉ። የነደደዉ ልቤም ለበቀል አደባ። ጉድጓዱ ተቆፍሮ ካለቀ በኋላ የደህንነት ሠራተኛዉ AK ጠመንጃዉን አንደኛዉ ወጣት አገጭ ላይ ቀስሮ በአፈሙዙ አንገቱን ቀና እንዲያደርግ እያስገደደዉ . . . “አየኸዉ የምትገባበትን ጉድጓድ” እያለ ወጣቱ ወገኔ ላይ ሲሳልቅበት ሰማሁና በሀይወቴ ለመጀመሪያ ግዜ ኢትዮጵያዊነቴን ጠላሁት። አጠገቡ የቆመዉና በቁሙ ሞቱን የሚጠባበቀዉ ሌላዉ ወጣት ወገኔ ደግሞ . . . ግደለኝ . . . ግደለኝ. . . ግደለኝ እንጂ! . . . ምን ትጠብቃለህ እያለ የጓደኛዉን ሞት በአይኑ ከሚያይ የራሱን ሞት የሚለምነዉን ቆራጥ ኢትዮጵያዊ ድምጽ ስሰማ ደግሞ 360 ዲግሪ ተገለበጥኩና ከደቂቃዎች በፊት የጠላሁትን ኢትዮጵያዊነት መልሼ ወድድ አደረኩት። የወያኔዉ ጨካኝ ነብሰ ገዳይ ፉከራና ቆራጡ ኢትዮጵያዊ ያደረጉት የቃላት ምልልስ እምባዬን ጎትቶ አመጣዉና ፊቴ እምባ በእምባ ሆነ። ያ ከግማሽ ሰዐት በፊት ሲጨፈርበትና ሲደነስበት የነበረዉ ዳስ ሰዉ የሌለበት ባዶ ቤት ይመስል ጭጭ አለ። እኔ ኤፍሬም ሰዉ አልገድልም፤ በእኔ እጅ የሰዉ ህይወት ይጠፋል ብዬ አስቤም አልሜም አላዉቅም። ያንን የህወሃት ቅጥረኛ በዚያች ሰዐት ባገኘዉ ኖሮ ግን ለመበቀል ሳይሆን ለሰዉ ልጅ ህይወት ክብር ስል እገድለዉ ነበር።
ድራማዉ እንዳለቀ ወደ ዉጭ ወጣሁና ድቅድቅ ጨለማ ዉስጥ ብቻዬን ቁጭ አልኩ። ሀሳብ. . . የትናንት ሀሳብ፤ የዛሬ ሃሳብ፤ የነገ ሀሳብ፤ የከረመ ሀሳብና ሁሉም ሀሳብ አንድ ላይ ተሰባስበዉ ወረሩኝ። ግራ ሲገባኝና መላቅጡ ሲጠፋኝ ግዜ ትንፋሼን ዋጥ አደረኩና አንቺ እማማ ብዬ አገሬን ተጣራሁ . . . አሁንም አሁንም ደግሜ ተጣራሁ። ህመሟ ብርቱ ነበርና አልሰማችኝም። አይዞሽ ይህ ቀን ያልፍና አንቺም ከህመምሽ እኔም ከማያባራዉ የሀሳብ በሽታ ድነን አዲስ ታሪክ እንጽፋለን ብዬ ከአገሬ ጋር ቃል ኪዳን ገባሁና ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ዳሱ ዉስጥ ከነበሩት አርበኞች ጋር ተቀላቀልኩ። እለቱን ሲያስጨፍረን የዋለዉ አደራ ባንድ “ነይ ደኑን ጥሰሺ” የሚለዉን ቆየት ያለ የመሀሙድ አህመድ ዘፈን ሲጫወት ልጅነቴ ትዝ አለኝና ከፍም እሳቶች ጋር መደነስ ጀመርኩ።
ጭልጋን ይዞ፤ጋይንትን ይዞ፤ የጎበዞቹን ጎራ ጃናሞራን ይዞ፤ ደምቢያን ይዞ፤ ወልቃይት ጠገዴን ይዞ፤ ላይ አርማጭሆንና ታች አርማጭሆን ይዞ ወዘተ . . .ድፍን ጎንደር የጀግኖች አገር ነዉ። አዎ! ወልቃይት ጠገዴ ከጀግናም የጀግና አገር ነዉ።ወልቃይት ጠገዴ ጎንደሬ አይደለህም ተብሎ ከተነገረዉ ከሃያ አራት አመታት በኋላ ዛሬም ህልዉናዉን ለወያኔ ፋሺስቶች አላስረክብም ብሎ ጎንደሬነቱን ለማረጋገጥ ሽንጡን ገትሮ የሚዋጋ የጀግኖች አገር ነዉ። ጎንደር የአፄ ቴዎድሮስ፤ የእቴጌ ምንትዋብ፤ የፊትአዉራሪ ገብርዬ፤ የአየለ አባ ጓዴና የጄኔራል ነጋ ተገኝ አገር ናት። ጎንደር ኢትዮጵያ ከሌለች እኛ የለንም ብለዉ ሙሉ ህይወታቸዉን ለትግል የሰጡ እነ ታማኝ በየነንና እነ አርቲስት ሻምበል በላይነህን ያበቀለች አገር ናት። ወላድ በድባብ ትሂድ. . . የጎንደር ማህፀን ዛሬም አልነጠፈም።
ዛሬ ይዤላችሁ የመጣሁት ጀግና ተወልዶ ያደገዉ አማራ ክልል ጭልጋ ወረዳ ልዩ ስሟ ጫኮ በምትባል ቦታ ነዉ። የገበሬ ልጅ ነዉ፤ እሱም ምኞቱ ገበሬ መሆን ነዉ። የሚኖረዉ መተማ ከተማ ዉስጥ ነዉ። ስሙ መሠረት ሙሌ ይባላል። ፈገግታ የማይለየዉ ፊቱ የዋህነቱንና ገራገርነቱን አፍ አዉጥቶ ይናገራል። ሲናገር ረጋ ብሎ ነዉ። አተኩሮ ላየዉ ሰዉ አይነ አፋር ይመስላል፤ የቁርጥ ቀን ሲመጣ ግን እንደ መሠረት ሙሌ ደፋር ሰዉ የለም። አይኑ እፊቱ ላይ ቆሞ ከሚያናግረዉ ሰዉ አይን ጋር ሲጋጭ አንገቱን ይሰብራል። እቺ የሰዉ አይን የመሸሽ በሽታ ደግሞ አበሾች ስንባል የሁላችንም በሽታ ናት። ጠይም ፊቱ ላይ እንደ ችቦ የተተከሉት የመሠረት ሙሌ አይኖች የሰዉን ዉስጥ ዘልቀዉ የሚያዩ ይመስላሉ። ሰዉነቱ ደንዳና ቁመቱ መካከለኛ ነዉ። ልቡ ግን ትልቅ ነዉ። አዎ መሠረት ሙሌ ልቡ ትልቅ ነዉ።
ዕለቱ ሰኞ ነዉ – ሰኞ ሚያዝያ 26 ቀን 2007 ዓም። የህወሃት የደህንነት ሰዎች አንድ ኮሎኔልና ሌሎች አራት ሰዎች ተገድለዋል በሚል ድፍን መተማን እያመሷት ነዉ። እያንዳንዱ የመተማ ነዋሪ በግድያዉ የተሳተፈ ይመስል በአጠገባቸዉ ያለፈዉን ሁሉ ወንድ፤ ሴት፤ ወጣትና ሽማግሌ ሳይለዩ ሁሉንም እያስቆሙ አጥንት ዉስጥ ዘልቆ የሚገባ ስድብ ይሰድባሉ፤ ይደበድባሉ ያስራሉ። በሠላም አዉለኝ ብሎ በጧት የተነሳዉ መሠረት ሙሌ የእህል ወፍጮዉን አስነስቶ የዕለት ስራዉን ለመጀመር ጉድ ጉድ ማለት ጀምሯል። ሴቶች እህላቸዉን ያስመዝናሉ። ሸክም የተራገፈለት አህያ ያናፋል። ነጋዴዉ፤ ደላላዉ፤ ገበሬዉና ሸማቹ ዋጋ ቀንስ ዋጋ ጨምር እያሉ ይንጫጫሉ። መተማ መደበኛ ስራዋ ላይ ናት።
“ቁም . . . እጅ ወደ ላይ . . . እንዳትነቃነቅ” የሚል ድምጽ የደራዉን የመተማ ገበያ በአንድ ግዜ ጭጭ አሰኘዉ። መሳሪያ ያነገቡ ፖሊሶችና ሲቪል የለበሱ የደህንነት ሰራተኞች ከመኪና እየዘለሉ ወርደዉ መሠረትን የፊጥኝ አስረዉ መኪናዉ ላይ ወረወሩት። ምነዉ? ምን አጠፋሁ . . . ዬት ነዉ የምትወስዱኝ? አለ መሠረት በሁኔታዉ እጅግ በጣም ተደናግጦ። አንድ አጠገቡ የነበረዉ የህወሃት ነብሰ ገዳይ . . . ዝም በል ብሎ በጥፊ አጮለዉና ለአርበኞች ግንቦት 7 የመለመልካቸዉን ሰዎች አድራሻና ስም ዝርዝር ካላመጣህ ዕድሜህ ከአንድ ጀምበር አያልፍም አለዉ።
መኪናዉ ዉስጥ ከተቀመጡት ሁለት ሰዎች አንደኛዉ አንሂድ ብሎ በእጁ ምልክት ሲያሳይ መሬት ላይ የነበሩት ፖሊሶች እየዘለሉ መኪናዉ ላይ ወጡና መሠረትንና ሌሎች ሦስት እስረኞችን የያዘችዉ ቶዮታ ሂሉክስ መኪና ፍጥነት እየጨመረች የመተማ ሁመራን መንገድ ተያያዘቸዉ። በሚቀጥለዉ ቀን ጧት ሲነጋጋ ሁመራ ደረሱና አራቱ እስረኞች እጃቸዉ እንደታሰረ ፖሊስ ጣቢያ እንዲቆዩ ተደረገ። ከምሽቱ ሦስት ሰዐት ሲሆን መሠረትና ጓደኞቹ እጅ ለእጅ እንደተሳሰሩ ጉዞ ወደ ተከዜ ወንዝ ሆነ። የዚህች ከንቱ አለም የመጨረሻ ጉዟቸዉ ነበር።
ዶማና አካፋ ያዙ እንጂ . . . ደግሞም ፈጠን በሉ ግዜ የለንም. . . አለ የነብሰ ገዳዮቹ አለቃ። ከሁመራ ፖሊስ ጣቢያ ወደ ተከዜ ወንዝ የሚያደርገዉ ጉዞ በህይወቱ የመጨረሻዉ ጉዞ እንደሆነ የተረዳዉ መሠረት . . . አንተዬ ልትገድሉን ነዉ እንዴ ብሎ ጠየቀ። ፊት ለፊቱ የነበረዉ ፖሊስ ከተቀመጠበት ዘልሎ ተነሳና . . .ዝም በል . . . አንተ የሴት ልጅ . . . ምን አስቸኮለህ ይልቅ የተጠየከዉን ጥያቄ መልስ አለዉና የያዘዉን የእጅ መከርቸሚያ ካቴና ፊቱ ላይ ወረወረበት። ካቴናዉ ሳይሆን ከዚያ ባለጌ አፍ የወጡት ቃላት ጅማቶቹ ድረስ ዘልቀዉ ገብተዉ መንፈሱን ጎዱትና መሠረት ለመጀመሪያ ግዜ ተስፋ ቆረጦ . . . ምንም የምሰጥህ መልስ የለኝም አለና አንገቱን ደፋ። . . . አንቺ ወላዲት አምላክ ምነዉ . . . ምን አደረኩሽ ብሎ ቀና ሲል እሱንና ሦስት ጓደኞቹን ለመዋጥ አፋቸዉን ከፍተዉ የሚጠባበቁትን አራት ጉድጓዶች ተመለከተ። አይኔ እያየ እዚህ ወስጥ አልገባም ብሎ ንግግሩን ሳይጨርስ ተከታታይ የጥይት ድምጽ ሰማ። ዞር ሲል ፖሊሶች አብረዉት ከታሰሩት ሦስት እስረኞች ዉስጥ አንዱን በእግራቸዉ እየገፉ የተቆፈረዉ ጉድጓድ ዉስጥ ሲጨምሩት አየ። ደቂቃዎች የቀሩት የሱ የራሱ ህይወት ሳይሆን በህወሃት ነብሰ ገዳዮች በግፍ የተገደለዉ የጓደኛዉ ህይወት አንገበገበዉ። አዘነ – በአይኑም በሆደም አነባ። “አይኔ እያየ እዚህ ወስጥ አልገባም” ብሎ የተናገረዉ የራሱ ድምጽ ጆሮዉ ላይ አቃጨለበት። መሠረት ሞት ፈርቶ አያዉቅም፤ ግን ህይወቱ የህይወትን ክቡርነት በማይረዱ ባለጌዎች እጅ እንድታልፍ አልፈለገም። ያ የንጹሃን ኢትዮጵያዉያንን ሰዉነት ማፍረስ የለመደዉ የህወሃት ጠመንጃ ወደሱ ከመዞሩ በፊት አንድ ነገር ማድረግ አለብኝ ብሎ ወሰነ። እጁ ከጓደኛዉ ጋር የታሰረበትን ገመድ በጥርሱ በጣጠሰዉና ከቀለሁ እንደተላቀቀ ጥይት ተወርዉሮ እግሬ አዉጭኝ ብሎ ጫካ ዉስጥ ዘልሎ ገባ። የህወሃት ነብሰ ገዳዮች የጥይት ናዳ ለቀቁበት፤ እሱ ግን ጫካ ጫካዉን ይዞ ወደማያዉቀዉ ቦታ ሩጫዉን ተያያዘዉ።
መሠረት- ቆራጥነቱና የልቡ ትልቅነት ጉልበት እየሆኑት ነዉ እንጂ ያ የሚጠላዉ የህወሃት ጥይት አካሉን በሳስቶ ወንፊት አድርጎታል። ሰዉነቱ ቁስል በቁስል ሆኗል። ከራሱ ሰዉነት እንደ ጎርፍ የሚፈስሰዉ ደም ጠልፎ የሚጥለዉ እስኪመስለዉ ድረስ አካሉ ደምቷል። ሩጫዉን ግን አላቆመም። ደም እንዳይፈሰዉ ጥይት የበሳዉን ቦታ ሁሉ በሁለት እጆቹ ሸፈነ። እንደኛዉ ቁስል ጋብ ሲልለት እጁን ከሱ ላይ እያነሳ ሌላዉን ቁስል ሸፈነ። ደሙ መፍሰሱን ግን አላቆመም። መሠረትም ሩጫዉን አላቆመም። መሠረት ሙሌ ህይወቱን ለማዳን ወደ ፊት የህወሃት ነብሰ ገዳዮች ደግሞ ወንጀላቸዉን ለመደበቅ ወደኋላ በተለያየ አቅጣጫ ሩጫቸዉን ተያያዙት። ሁለቱም አግሬ አዉጭኝ አሉ።
መሠረት ሞትን እየሸሸ መሆኑን ነዉ እንጂ ከሞት ለመራቁ ምንም ዋስትና አልነበረዉም። ደግሞም መሮጡን ብቻ ነዉ እንጂ ወዴት እንደሚሮጥ አያዉቅም ነበር። ከኋላዉ የሚከተለዉ ማንም ሰዉ እንደሌለ ቢረዳም ከፊት ለፊቱ ህይወቱን የሚታደግለት ሰዉ እስኪያገኝ ድረስ ሩጫዉን ቀጠለ። ጧት ጎህ ከመቅደዱ በፊት “ጠጠዉ በል” የሚል ድምጽ ሲሰማ ያ ሁሉ ሩጫዉ መልሶ ሞት ዉስጥ የከተተዉ መሰለዉና ደነገጠ። ሩጫዉን እንዳይቀጥል ቁም ያሉት ሰዎች ከበዉታል። እሺ ብሎ እንዳይቆም ሞትን አልቀበልም ያለዉ ልቡ አሁንም እንደደነደነ ነዉ። ትንፋሹን ሰበሰበና. . . ማናችሁ እናንተ ብሎ ያቆሙትን ሰዎች ጥያቄ ጠይቆ መልሱን ሳይሰማ ተዝልፍለፎ መሬቱ ላይ በግንባሩ ተደፋ።
የኤርትራ ድንበር ጠባቂ ወታደሮች መሠረትን አንድ ወር ሙሉ በህክምና ሲንከባከቡት ቆዩና እሱ እራሱ በጠየቃቸዉ መሠረት ሃሬና ወስደዉ ለአርበኞች ግንቦት 7 አስረከቡት። መሠረት ሙሌ ጥቅምት 7 ቀን ከተመረቁት አርበኞች ዉስጥ አንዱ ነዉ። ለዚህ ጀግና ያቀረብኩለት የመጨረሻ ጥያቄ . . . ሊገድሉህ የነበሩትን የህወሃት ሰዎች አሁን ብታገኛቸዉ ምን ታደርጋቸዋለህ የሚል ጥያቄ ነበር። ነጻ አወጣቸዋለኋ! አለኝና ጭፈራዉ ዉስጥ ዘልሎ ገባ። አርግጠኛ ነኝ መሠረት ሙሌ አንድ ቀን ሁላችንንም ሸገር ላይ ያስጨፍረናል። ቸር ይግጠመን።
ኤፍሬም ነኝ ከአርበኞች መንደር
ebini23@yahoo.com

የህወሓት አገዛዝ የቀድሞው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት የነበሩትን እየለቀመ እያባረረ ነው

October 31,2015
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ እንደዘገበው) ህወሓት በ1983 ዓ.ም መላ አገሪቱን በነፍጥ እንደተቆጣጠረ በሁለት ያለፉ የኢትዮጵያ መንግስታት ከፍተኛ የህዝብ ሀብት፣ ዕውቀትና ጉልበት ፈሶበት ለዘመናት በስንት ልፋትና ጥረት የተገነባውን የአገር መከላከያ ሰራዊት ባደረበት ጭፍን ጥላቻና ቂም ብቻ ተመስርቶ “የደርግ ነው” በሚል ሰበብ ባንድ ጀምበር ንዶ ማፈራረሱን አገር ያወቀው ፀሃይ የሞቀው ሀቅ ነው፡፡
(ፎቶ ፋይል መፍቻ) የሕወሓት መንግስት በስማቸ እየነገደ ገንዘቡን የሚበላባቸው የኢትዮጵያ መከላከያ ወታደሮች በሱማሊያ ሬሳቸው ሲጎተት::

(ፎቶ ፋይል መፍቻ) የሕወሓት መንግስት በስማቸ እየነገደ ገንዘቡን የሚበላባቸው የኢትዮጵያ መከላከያ ወታደሮች በሱማሊያ ሬሳቸው ሲጎተት::



ከበረሃ የመጡ ድኩማን ታጋዮቹን ለሙያው የሚመጥን ምንም አይነት ዘመናዊ ዕውቀት ሳይኖራቸው የጀነራልነት ማዕረግ በማሸከም በአየር ኃይሉና በምድር ኃይሉ ውስጥ በሚገኙ የአዛዥነት ቦታዎች ላይ እነሱን ብቻ አስቀምጦ ስልጣኑን ለመጠበቅ ብቻ እንዲተጉለት በማድረግ የአገራችንን ብሄራዊ ደህንነት አደጋ ላይ ጥሎት ይገኛል፡፡

ህወሓት የተባለው ዘረኛ ቡድን ውስጡ በቂምና በጥላቻ ብቻ ተሞልቶ ያፈራረሰውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት አደጋ ባንዣበበበት ጊዜ ጥሪ በማድረግ መልሶ ለመሰብሰብ የሞከረ ሲሆን ከጦርነቱ በኋላ ደግሞ አብዛኞቹን ከተጠቀመባቸው በኋላ እንደገና አባሯቸዋል፡፡

አሁን ደግሞ አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ እያፋፋመው ከሚገኘው የአርበኝነት ትግል ጋር በተያያዘ ከትግራይ ተወላጅ የህወሓት ተጋዮች ውጭ በሆኑ ወታደራዊ አዛዦች ላይ ዕምነት በማጣቱ የመከላከያ ኃይሉን የማጥራት የወቅቱ አንገብጋቢ ውሳኔውን የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላትን በማባረር ተግባራዊ ማድረግ ጀምሯል፡፡

ቂምና በቀሉ መቸም የማይበርድለት ህወሓት በተደጋጋሚ የደም ቁማር ሲቆምርባቸው ከኖሩት የተባረሩ የቀድሞው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት አብዛኞቹ የአርበኝነት ትግሉን በመቀላቀል ላይ ናቸው፡፡

Wednesday, October 28, 2015

Andargachew Tsege ‘fears he will die in Ethiopia’

October 27,2015
A British man locked up for more than a year in Ethiopia fears he could die in prison.
Andargachew “Andy” Tsege, a father-of-three, has been detained in the country since he was removed from an airport in Yemen in June 2014.UK “stands shoulder to shoulder” with Ethiopia
Legal charity Reprieve said the 60-year-old asked the British Government to ensure that he is buried in England and told his children to “be brave” during a recent visit by the UK ambassador.
Mr Tsege, a prominent critic of Ethiopia’s ruling party, was sentenced to death in his absence in 2009 for allegedly plotting a coup – charges he and others deny.
The trial has been described as “lacking in basic elements of due process”.
He fled Ethiopia in the 1970s, seeking asylum in the UK in 1979.
Maya Foa, head of the death penalty team at Reprieve, said: “It is tragic that he now feels the only way he will return home to Britain is in a coffin.
“The Foreign Office must urgently push for his release, so he can return to his partner and children in London before it’s too late.”
Last week, Foreign Secretary Philip Hammond discussed the case with the Ethiopian Foreign minister.
Mr Hammond said: “I raised the case of Andargachew Tsege with the Ethiopian Foreign Minister during our meeting on October 21, and made it clear that the way he has been treated is unacceptable.
“I welcome the improvement in access to him, following the British Government’s intervention, but it must be more regular and it must include access to a lawyer.
“I am still not satisfied that Mr Tsege has been given an ability to challenge his detention through a legal process, and this is something we are continuing to pursue.
“The Foreign Office will continue to provide consular support to Mr Tsege and his family.”
Source: BT.com

Sunday, October 25, 2015

የህወሃት ባለስልጣናት በከፍተኛ ደረጃ ዶላር እያሸሹ ነው

October 25, 2015

በሰሜን አሜሪካ በህግ ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድ ለአንድ ዶላር በ23 ብር እየቀየሩ ሃብታቸውን በማካበት ላይ እንደሚገኙ ታወቀ።
የኢህአደግ ስረአት ባለ ስልጣኖች ሃብታቸውን ከውስጥ ሃገር ለማውጣት እየተጠቀሙት ያለውን ስልት የኢትዮጵያ ባንኮዎች ከመጉዳት ባለፍ በአሁኑ ወቅት የአገሪቱን ኢኮኖሚ ከባድ ችግር ውስጥ አስገብተውት እንደሚገኙ የገለጸው መረጃ: በአሁን ጊዜ የኢህአዴግ ባለ ስልጣኖች በሙስና ያጠራቀሙት ሃብት ወደ ዉጭ በማጓጓዝ ላይ ተጠምደው ባሉበት ግዜ ከሰሜን አሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ ከመጠን በላይ በኮትሮ ባንድ ንግድ ለአንድ ዶላር በ23 ብር እንመነዝርላችሓለን በማለት በህዝብ ሃብት በመጫወት ላይ ኣንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።
TPLF Ethiopian Leaders
መረጃው አክለዉ እንዳመለከተው በአሁኑ ጊዜ፡ በዋሽንግተን፤ በዱሲ፤ ስያትል፤ ዴንቭር፤ ሚኒያፖሊስ፤ አትላንታ፥ ቺካጎ፤ በሂውስተን፤ ኦሃዮ፤ ፓርትላንድ፤ ላስቬጋስ፤ ካልፎርኒያ እንዲዚሁም በተለያዩ ከተሞች በአሪዞና በተዘረጉት መረቦች መረጃ ዶላር በኮትሮ ባንድ ንግድ በ23ብር እየተመነዘር መሆኑን መረጃው አስታውቀዋል።
በመጨረሻም አንድ የአሜሪካ ዶላር በህጋዊ መንገድ ብ20.85 ብር እየተመነዘር ቢሆንም በሌቦች የኢህአድግ የገዢው ስረአት ባለ ስልጣናት ግን ዶላር ያለ ህጋዊ መንገድ የኢትዮጵያ የውጪ ምንዛሬ ያለ አግባብበ በመቀየራቸው የተነሳ የሃገር ውስጥ መንዛሪ ከፋተኛ እጥርት እያጋጠመ እንዳለ የተለያዩ ህዝቦች በመግለፀ ላይ ይገኛሉ::

Friday, October 23, 2015

እናመሰግናለን! የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች

October 23, 2015
Thank You! Zone9 bloggers
በድንገት ከያለንበት ተይዘን እንደታሰርነው አፈታታችንም ግራ የሚያጋባ ነበር፡፡ ተመሳሳይ ክሶች ቀርበውብን እያለ ግማሾቻችን ‹ክስ ተቋርጦላችኋል› ተብለን ተፈታን፣ ግማሾቻችን ደግሞ ‹ነፃ ናችሁ› (ከሳሽ በነፃነታችን ላይ ይግባኝ መጠየቁ እንዳለ ሁኖ) ተብለን ይሄው ወጥተናል፡፡ ቀሪ ክስ ይዘን በዋስ ወጥተን እየተከራከርንም ያለን አለን፡፡ በዚህ ሁሉ መሃል የሁላችንም ዕምነት ግን አንድም ቀን ሊያሳስረን የሚገባ ወንጀል አለመፈፃችን ማመናችን ነው፡፡ መፈታታችን ጥሩ ሁኖ፤ መታሰር በፍፁም የማይገባን ነበርን፡፡ መፃፋችን እና ሕግ እንዲከበር መጠየቃችን ሀገሪቱ አገራችን እንድትሻሻል እና ሁላችንም ዜጎች የተሻለ ህይወት አንዲኖራቸው ከመሻት ባለፈ ሌላ ነገር አልነበረውም/የለውም፡፡ ነገር ግን ይህን በማድረጋችን ተገርፈናል፣ ተዘልፈን-ተሰድበናል፣ ታስረናል ተሰደናልም፡፡ ይህ በፍጹም አይገባንም ነበር፡፡
የእኛ መታሰር ፖለቲካዊ ንቃት የፈጠረላቸው ሰዎች እንዳሉ ሲነግሩን ደስ ይለናል፡፡ በእኛ መታሰር ምክንያት ለመጠየቅና ለመፃፍ በጣም እንደሚፈሩ የሚነግሩን ሰዎች ስናገኝ ደግሞ እናዝናለን፡፡ የመታሰራችን ጉራማይሌ ስሜት እንደዚህ ነው፡፡ ሳይገባን በመታሰራችን የነቁ መኖራቸውን በማወቃችን የምነደሰተውን ያክል፤ ሳይገባን በመታሰራችን የተሰበሩና ከተዋስኦ መድረኩ የራቁ እንዳሉ ስናውቅ እጅግ እናዝናለን፡፡
መታሰር በደል ነው፡፡ ብዙ ነገር ያጎድላል፡፡ መታሰር መልካም ነው፡፡ ብዙ ነገር ያስተምራል፡፡ እኛ በመታሰራችን ሀገራችን የበለጠ እንድናውቃት ሁነናል፡፡ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ ነፃነት አሁንም ብዙ ዋጋ እንደሚያስከፍል ተረድተናል፡፡ ሕግን መከታ አድርገው የኖሩ ‹ስም የለሽ› ዜጎች ሕጉ ሲከዳቸውና እነሱ ላይ ‹በላ› ሲያመጣባቸው ታዝበናል፡፡ ከሁሉም በላይ ፍትህ የሌለባት ሀገር ለዜጎቿ የማትመችና አገር እንደሆነች አይተናል፡፡
በእስራችን ወቅት የተለያዩ በደሎች በተቋም ደረጃ ደርሰውብናል፡፡ ግን አገር ነውና ከይቅርታ የሚያልፍ አይደለም፡፡ ለበደላችሁን አካላት እናንተ ይቅርታ ባትጠይቁንም፤ እናንተ የፈለጋችሁትን ባለማድረጋችንና ሕግን መሰረት አድርገን በመኖራችን ስላስከፋናችሁ እባካችሁ ይቅር በሉን፡፡
በዚህ ሁሉ መሃል ግን እናንተ አላችሁ፡፡ ጓደኞቻችንም ናችሁ፤ ዘመቻ አድራጊዎችም ናችሁ፤ ቤተሰቦቻችንም ናችሁ፤ ጠያቂዎቻችንም ናችሁ፤ ጠበቆቻችንም ናችሁ፣ የመንፈስ አጋሮቻችንም ናችሁ ርቀት ሳይገድባች የጮሃችሁልን አለም አቀፍ የመብት ጠያቂዎችም ናችሁ … በመታሰራችን የተረዳነው አንዱ ትልቅ ነገር የናንተን መልካምነት፣ የናንተን አጋርነት እና የናንተን የማይሰለች ድካምና ፍቅር ነው፡፡ እናንተ ባትኖሩ ‹አጭሩ› የእስር ጊዜያችን ይረዝምብን ነበር፤ ‹ቀላሏ› እስር ትከብድብን ነበር፡፡ ምስጋና ለናንተ፤ እስራችን ‹አጭር› – ፈተናችን ‹ቀላል› እንዲሆን አድርጋችሁልናልና፡፡
እናንተ ወዳጆቻችን ለሁሉም ነገር – እልፍ ምስጋና
እናመሰግናለን!
የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች

Wednesday, October 21, 2015

ሶማሊያ የሚገኙ የጦር ሠራዊት አባላት ሲበደሉ ያመናል !

October 21, 2015
def-thumbየተባበሩት መንግሥታት ማኅበር የሚሰጠው ገንዘብ ህሊናቸውን በሰወራቸው፤ የህወሓት አባላት በሆኑ ጄኔራሎች አዝማችነት ሶማሊያ የገባው ኢትዮጵያዊ ድሃ ወታደር እጣ ፈንታ በጣም አሳዛኝ ደረጃ ላይ ደርሷል። በየእለቱ ኢትዮጵያዊያን ወታደሮች እየተገደሉ፤ አስከሬናቸው በጎዳናዎች እየተጎተተና እየተቃጠለ ነው። ሶማሊያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ሠራዊት አባላት ወገኖቻችን ናቸውና በእነርሱ ላይ የሚደርሰው ስቃይ ይሰማናል፤ ሲበደሉ ያመናል፤ ጭንቀታቸው ይጨንቀናል። ወገኖቻችን ናቸውና የደህንነታቸው ጉዳይ ያገባናል።
የህወሓት ጄኔራሎች ሙሉ ትኩረታቸው ያለው በእያንዳንዱ ወታደር ስም ከተባበሩት መንግሥታት በሚያገኙት ገንዘብ መጠን ላይ ነው። ለሶስት ሣምንታት ብለው የገቡበት ጦርነት እነሆ አስር ዓመታት አስቆጥሯል። አንዱ የገቢያቸው ምንጭ ነውና ጦርነቱ ለሌላ አስር ዓመታት ቢራዘም ለእነሱ ደስታቸው ነው። ኢትዮጵያዊው ምስኪን ወታደር ግን አዛዦቹ እንዲያልቅ በማይፈልጉት ጦርነት ውስጥ ገብቶ መስዋዕትነት ይከፍላል፤ ሲወድቅ የሚያነሳው የለም፤ መስዋዕት ሲሆን የክብር አሸናኘት የለውም፤ ቤተሰቦቹም ይኑር ይሙት አያውቁም። ይህ ሁላችንንም ሊያስቆጣ የሚገባ ግፍ ነው።
ኢትዮጵያን ለመታደግ ብሎ የዘመተን ወታደር ስለኢትዮጵያ ግድ በማይሰጣቸው፤ ጥቅማቸውን ብቻ በማሳደድ ላይ ያሉ አዛዦች ቸልተኝነት ምክንያት ለስቃይ፣ ሰቆቃና ውርደት መዳረግ የለበትም። በሶማሊያ በሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደሮች ላይ የሚደርሰው በደል በሁላችም ላይ የደረሰ በደል ነው፤ በእነርሱ ስብዕና ላይ እየደረሰ ያለው ውርደት በአገራችን ላይ የደረሰ ውርደት ነው።
የጦሩ አዛዦቹ በወታደሩ ስቃይና ሞት ከብረው የከተማ ድሆችን እያፈናቀሉ ሕንፃዎችን እየገነቡ፤ የባንኩን፣ የኢንሹራንሱን፣ የገቢና ወጪ ንግዱን እያጧጧፉ ነው። የወታደር ልብስ ቢለብሱም፤ “ጄኔራል እከሌ” ተብለው ቢጠሩም በተግባር መጥፎ ነጋዴዎች እንጂ ወታደሮች አይደሉም። እነዚህ የስም ጄኔራሎች በጦርነት ውስጥም የሚታያቸው ንግድና ገበያ ነው። በእንደነዚህ ዓይነቶች አዛዦች ተመርቶ ጦርነትን ማሸነፍ አይቻልም።
አርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ በህወሓት የጦር አዛዦች ብቃት ማነስ፣ ስግብግብነትና ቸልተኝነት ሳቢያ በሶማሊያ እየሞቱ፣ እየቆሰሉ፣ አስከሬናቸው እየተዋረደ ስላለው ኢትዮጵታዊያን የሚሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል።
ከሶማሊያ ውጭም የኢትዮጵያ ወታደር የሚገኝበት ሁኔታ እጅግ አሳዛኝ ነው። በተለይም በሀገር ውስጥ የኢትዮጵያ ወታደር እንደ ስሙ “የአገር መከላከያ ሠራዊት” በመሆን ፋንታ ወገንን ማጥቂያ ሠራዊት እየሆነ ነው፤ አገርን በመከላከል ፋንታ ወገንን ማጥቃት የሠራዊቱ የዕለት ተዕለት ተግባር ሆኗል። ለዚህ አሳፋሪ ተግባር ሠራዊቱ ራሱ መላ ሊፈልግለት ይገባል።
አርበኞች ግንቦት 7 እየታገለ ያለው ሠራዊቱን ከሚገኝበት ከዚህ አሳፋሪ ሁኔታ ለማውጣትም ጭምር ነው። ሠራዊቱ የአዛዦቹ መገልገያ መሣሪያ መሆኑ ማብቃት አለበት። ሠራዊቱ ወገንን ማጥቂያ መሆኑ ማክተም አለበት። ሠራዊቱ ወደ ውጭ አገራት ለግዳጅ ሲላክ ተገቢውን ክብር ሊሰጠው፤ ጥቅማ ጥቅሞቹም ሳይሸራረፉ ሊያገኝ ይገባል። የሠራዊቱ አባላት እየደኸዩ፣ ቤተሰቦቻቸው እየተራቡና እየታረዙ አዛዦቹ በሀብት ላይ ሀብት የሚያጋብሱበት ሁኔታ ማብቃት አለበት። ይህ አዋራጅ የሠራዊት አያያዝ መቀየር አለበት፤ መቀየር ደግሞ ይቻላል።
እያንዳንዱ የሠራዊት አባል በግል የጠራ ፀረ-ህወሓት አገዛዝ አቋም ይያዝ፤ ከሚመስሉት ወዳጆቹ ጋር ውስጥ ውስጡን ይምከር፤ አርበኞች ግንቦት 7 ጋር የምስጢር ግኑኝነት ለመመስረት ይጣር፤ ጦሩ ውስጥ እያለ ሥርዓቱን የሚዳክሙ ተግባራትን ይፈጽም። ህወሓትን ለማዳከም የሚደረግ ጥረት ትንሹም ትልቅ ዋጋ አለው። ሠራዊቱ የህወሓት መገልገያ አለመሆኑ ማስመስከሪያ ወቅት አሁን ነው። የህወሓት አምባገነን አገዛዝን ከውስጥም ከውጭም ሆነን እንፋለመዋለን፤ እንደምናሸንፍ ጥርጥር የለውም።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

ወያኔ የኑሮ ውድነት ለመደበቅ ቢሞክርም ሊደበቅ አልቻልም፣

October 21, 2015
በሃገራችን በኢሀዴግ ስረአት ብልሹነት ምክንያት የተነሳ የህዝባችን የኑሮ ውድነት ከግዜ ወደ ግዜ እየተባባሰና በተለይም ዝቅተኛ የኢኮኖሚ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ካለው የገበያ ውደነትና የሚፈለገው የእህል አይነት ባለ ማገኘታቸው በረሃብና በችግር ውስጥ ሆነው ኑራቸውን ይመራሉ።
ይሁን እንጂ የሃገሪቱ መሪ ተብየው የኢህአዴግ ሰረአት በተለያየ ቦታዎች የሚገኙ ህዝብ በቂ ምርት ባለ መኖሩ የፈጠረዉ ዋጋ ግሽበት እየተሰቃየ ባለበት ውቅት የሃገሪቱ ኢኮኖሚ በዕደገት ጎዳና ላይ እየገሰገስን ነው በማለት በሞተ ቃላት ሲናገር ይሰማል።
በተለይም በአሁን ሰአት ከዝናብ መጥፋት ጋር ተያይዞ በርካታ ዜጎች በቤታቸው ውስጥ እየሞቱ ምንም አይነት የመንግሰት ደጋፍ ያለመደረጉ እንዲሁም በተለያየ የሃገሪቱ ክፍል ከግዜ ወደ ግዜ በፍጠነት እየተባባሰ ያለዉ ኑሮ ዉድነት ትኩረት ሳይሰጠው ህዝባችን አልተቸገረም እያለ በቴሌቭዥን መስኮት መናገሩ ለህዝብ ያልቆመ መንግስት መሆኑን አሰረጂ ነገር ስለ ሆነ ህዝብ በገዡዉ የኢህኣዴግ ስርዓት ያለው እምነት ሙሉ በሙሉ ተሟጦ ተስፋ ቆርጦ ይገኛል።
በተግባር በመስራት ሳይሆን በማሰመሰል የሚታውቀው የኢህአደግ ስርአት ህዝብ በልመና በየመንገዱ ሴት ወንድ ትንሸ ትልቅ ሳይል በየሁቴል ቤቱ የተረፈ ምግብ ለመግዛት ወረፋ ይዞ መገኘቱ የሃገሪቱ የኢኮኖሚ ውድቀትን አመላካች መሆኑን ያስገነዝባል።
ሆኖም ተጎጅው ህብረተሰብ ችግሩን በተደጋጋሚ ቢናገርም ሰሚ አካል ያለማገኘቱ ብሶቱንና ሀዘኑ ከባድ እንዲሆን አድርጎት እያለ ባለሃብቶቹ ደግሞ ደስ ባላቸው ዋጋ በገበያ እየሸጡ በድሃው ህዝብ ላይ የሚፈልጉትን ያህል ዋጋ ስለሚጩንበት ህብረተሰቡ ለመግዛት ከአቅሙ በላይ ሆኖበት በችጋርና ረሃብ እየተሰቃየ ይገኛል።
የመንግሰት ሰራተኛ በተመለከተ ከሚከፈለው ገንዘብ ማነስ የተነሳ የወር ክፋያው የእህል መግዣ የወጥ (ማተሪያል) ማለትም የሽንኩርት የዘይት የመሳሰሉ ለሟሟላት አቅም ባለመኖሩ ምክንያት የሚከፈለው የቤት ኪራይ በማጣቱ ወደ ሌላ ሁለተኛ ሃገር በመሰደደ ላይ ይገኛል።
ስለ ሆነም የኢህአደግ ሰረአት ህዝባችንን በቀን ሶሰት ግዜ መመገብ ችለናል እያለ በየመድረኩ በባዶ ቃላት ለብዙ አመታት እየተናገረ ቢሆኑም ህዝብ ግን በተፈጠረው የኑሮ ወድነት የተነሳ መሬቱን ተረከቡኝ ግብር መከፈል አልቻልኩም በማለት በመንግሰት ላይ ያለውን ተቃውሞ በመግለጽ ላይ ይገኛል።
ሰሞኑን የኢህአደግ አመራሮዎች በአዲስ አበባ አንድ የእህል መጋዘን ባደረጉት የገበያ ጉብኝት ለህዝብ በሰጡት መልስ ምንም አይነት የዋጋ ውደነት የለም ሲሉ ተሰምተዋል ተጠቃሚው ህዝብ ግን ይህ የተሰጠው ምላሸ እጅግ አድረጎ እንዳሰቆጣው ለመረዳት ተችሏል።
ህብረተሰቡ ገንቢ የሆኑ ምግቦችን ማለትም እንደ ስጋ ቅቤ መጠቀም ከተው ብዙ አመት ያስቀጠረ በመሆኑና በየክልሉ እና በአዲሰ አበባ ከተማ የሚገኙ የምግብ ቤቶች የሚሰሩ ባለሃብቶች ተጠቃሚ ካለመኖሩ የተነሳ በተጨማሪም ችግሩ እየተባባሰ በመሄዱ ምግብ ቤታቸውን ለመዝጋት ተገደዋል።

Tuesday, October 20, 2015

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ለሁለተኛ ጊዜ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት አስመረቀ

October 20, 2015
የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ
Professor Berhanu Nega with Patriotic Ginbot7 fighters
አርበኞች ግንቦት 7 በሁለት ድርጅቶች ማለትም በኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር እና በግንቦት 7 ንቅናቄ ውህደት ጥር 2 ቀን 2007 ዓ.ም ከተመሰረተ በኋላ ከትናትና በፊት እሁድ ዕለት ጥቅምት 7 ቀን 2008 ዓም ለሁለተኛ ጊዜ ብዛት ያላቸውን አርበኛ ታጋዮች ለሦስት ወራት አሰልጥኖ አስመርቋል፡፡
እነዚህ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሁለተኛ ዙር ተመራቂ አርበኛ ታጋዮች ለሦስት ተከታታይ ወራት የተሰጣቸውን የፖለቲካ፣ የወታደራዊ እና ሌሎች ተያያዥ የሆኑ የመረጃና ደህንነት ትምህርቶችን በሚገባ ወስደው በሁሉም መስክ አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ ነው ሊመረቁ የቻሉት፡፡
እጅግ በጣም ደማቅ በሆነ ስነ-ስርዓት በተከናወነው የምረቃ በዓል ላይ ከተለያዩ ቦታዎች ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች የታደሙ ሲሆን የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር አርበኛ ታጋይ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የድርጅቱ የትምህርትና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ታጋይ ተስፋሁን ተገኝ ንግግር በማሰማት ለተመራቂ አርበኛ ታጋዮች መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ከውህደቱ ኋላ የመጀመሪያውን ዙር ሰልጣኞች ያስመረቀው ግንቦት 2 ቀን 2007 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል፡፡
Patriotic Ginbot7 fighters

Monday, October 19, 2015

የማእከላዊ ምርመራ የማሰቃየት ምርመራ መዘዝ - በጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ላይ

October 19,2015
የ2007 አገር አቀፍ ምርጫ መቃረብን ተከትሎ መስዋእት ከሆኑት  የዞን ዘጠኝ ጦማር አባላት ውስጥ የሽብር ክሱ ወደ ወንጀል ክስ ተቀይሮ ዛሬም በግፍ እስር በብቸኝነት የሚገኘው በፍቃዱ ዘ ኃይሉ አመጽ ለመቀስቀስ አስበህ ነው የጻፍከው የተባለውን ጽሁፍ እንዲከላከል ተወስኖበታል፡፡ ይህ የአመጽ መቀስቀስ የተባለው ጽሁፍ ራሱን ሳይሆን የበፍቃዱን የማእከላዊ ምርመራ ቃል ብቻ የተመለከተው ፍርድ ቤቱ ቃሉን ብቻ መሰረት በማድረግ ይከላከል በማለት የማእላዊ ምርመራን በማሰቃየት ውስጥ የተሰጠ ቃል ተቀብሎታል ማለት ነው ?

በአስገዳጅ ሁኔታ የተገኘ ማስረጃ እንደማስረጃ አይቆጠርም የሚለው የሕጎች ሁሉ የበላይ ነው የሚገባለው እና በፍቃዱ ከጓዶቹ ጋር ሆኖ ይከበር! ሲል የነበረው ሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 19.5 እንዲህ ይላል

‹‹የተያዙ ሰዎች በራሳቸው ላይ  በማስረጃነት ሊቀርብ የሚችልየእምነት ቃል እንዲሰጡ ወይም ማናቸውንም ማስረጃ እንዲያምኑ አይገደዱም፡፡ በማስገደድ የተገኘ ማስረጃ ተቀባይነትአይኖረውም፡፡››

ከወራት በፊት የጦማርያኑን እስር አንደኛ ዓመት አስመልክቶ የመብት ጥሰቶችን ዞን ዘጠኝ ጦማር ባስታወሰበት ወቅት በበፍቃዱ የደረሰበት የማሰቃየት ወንጀል እንዲህ ገልጾት ነበር ፡፡

‹‹ማዕከላዊ ምርመራ በቆየሁባቸው ቀናት ከእሁድ በስተቀር ጠዋት ከሰአትማታ እየተጠራሁ በዛቻ በአጸያፊ ስድብ ጭካኔ የተሞላበት ግርፊያ ጥፊና እርግጫ አንዲሁም ከአቅሜ በላይ የሆነ ስፓርት እየሰራሁቃሌን እንድሰጥ ተገድጃለሁ፡፡ የተያዝክበትን ድብቅ አጀንዳ ንገረን በማለት ራሴን እንድወነጅል ተገድጃለሁ፡፡
  1. መርማሪው በመጀመሪያ ቀን ምርመራ በጥፊ መማታት የጀመረ ሲሆን እያንዳንዱን ጥያቄ ከጠየቀኝ በኋላ በጥፊ ይመታኝ ነበር
  2. የዞን9 ዓላማ ጠይቆኝ ስነግረው ድብቁን አውጣ በማለት መሬት ላይ አንድቀመጥ እና ያደረኩትን ነጠላ ጫማ እንዳወልቅ አዞኝ በኮምፒውተር ገመድ እግሬን መግረፍ ጀመረ፡፡ በተጨማሪም በሆዴአንተኛ በማዘዝ እና እግሬን አጥፌ ከፍ አንዳደርገው በማድረግ ውስጥ እግሬን ገርፎኛል፣ግርፊያው ውስጥ እግሬን ሲለበልበኝ ነበር ፡፡
  3. ድብቁን አጀንዳህን ካልተናገርክ ነገ እዘለዝልሃለሁ በሚል አስፈራርቶኛል፡፡
  4. ድምጽ እንዲያፍን ሆኖ ወደተሰራው የስብሰባ አዳራሽ ተወስጄ በጥፌ እየደበደቡኝ የዞን9አላማ ተናገር ተብዬ ተደብድቤያለሁ፡፡ ስቃዬ ሲበዛብኝም የፈጠራ ታሪክ እንዳወራ ተገድጃለሁ፡፡ እኔ የምጽፈው ኢትዮጵያ ውስጥ አብዬት ለማስነሳት ነው ብዬ እንድፈርምም አስገድደውኛል››
  5. በምርመራ ወቅት እጄ በካቴና እነደታሰረ ለሰአታት ቁጭ ብድግ አንድል ተገድጃለሁ፡፡
  6. መርማሪው በአንድ ወቅት አራት የዞን9 አባላት ሆናችሁ ስለአላማው የተወያያችሁትን በቃል መስጫው ክስ ላይ ልጽፍ ነው ሲለኝ አንደዛ አይነት ውይይት ማድረጋችንን አላስታውስም ስለው እንዴት አታስታውስም ብሎ በጥፊ መማታት ጀመረ። በተደጋጋሚ ከመደብደብም በላይ እስክስታስታውስ እዚሁ ታድራታለህ በማለት ድብደባው በመቀጠሉ አስታውሳለሁ ብዬ ተገላገልኩ ፡፡ የሰጠሁት ቃል ላይም እንደፈለገው አድርጎ ጻፈው፡፡  እኔም በድብደባ ብዛት መርማሪው አለ ብሎየጻፈውን ፈርሜያለሁ ፡፡
  7. ዞን9 ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት የሌለው ከሆነ ይህንን ህዝብ አንዴት ነው ነጻ የምታወጡት በሚል ሲጠይቁኝ የነጻ አውጪነት ሚና የለንም ስላቸው ከወንበሬአንድነሳ አዘዙኝ፡ ከዚያም በቆምኩበት ግራ ብብቴን እና እጄን በአንድ እጁ አንዳልወድቅ ወጥሮ ይዞ በእግሩ ጭኔን በሃይል ደበደበኝ ፡፡ ከድብደባው በማስከተል ደግሞእግሬ መሃል እግሩን በማስገባት ወደግራ እና ወደቀኝ በመምታት ተዘርጥጬ እንድቆይ በማድረግ እጄን ወደላይ አድርጌ እግሬ ግራና ቀኝ ተዘርጥጦ ( በተ<a></a>ለምዶ ስፕሊት ሚባለው) በግራ እና ከቀኝ በመደብደብ እጄን ወደላይ አድርጌ እነድመረመር ተደርጌያለሁ፡፡ከዚህ ምርመራ በኋላ ለሁለት ቀን እያነከሰኩ ነበር፡፡››
በፍቃዱ ሃሳቡን በነጻነት በመግለጹ ብቻ እንደወንጀለኛ ተቆጥሮ እስካሁንለ542 ቀናት አግባብ ባልሆነ እስር ላይ ይገኛል፣ በዚህ ሁኔታ የተሰጠ ቃል ተቀባይነት ማግኘት ስለማይገባው በፍቃዱ ሃይሉእሮብ ከቤተሰቡ ጋር ሊቀላቀል ይገባል ፡፡

A Government-in-Exile for Ethiopia?

October 19,2015
by Alemayehu G. Mariam
Foreword to a “government-in-exile for Ethiopia”A Government-in-Exile for Ethiopia?
A few weeks ago, I gave an interview to an Ethiopian civic group on the topic of “government in exile” under international law.
I was asked to comment on whether the idea and practice of “government in exile” is cognizable under international law.
The implicit question was whether Ethiopians could constitute a legitimate “government-in-exile” in opposition to the Thugtatorship of the Tigrean People’s Liberation Front (T-TPLF) lording over Ethiopia today.
A word or two on the aim of this commentary.
The aim of my analysis here is not to endorse or discredit a particular group planning or purporting to be a “government-in-exile” for Ethiopia.  Nor is it my aim to make a political point against the T-TPLF and show my opposition to their regime, their endless crimes against humanity, their bottomless corruption, their ignorant arrogance and sheer incompetence as a governance body.
I have done that with ferocious tenacity every Monday over the past nine years.
The aim of my commentary is to shed light on a question of broad interest among Ethiopians from my legal perspective.
As a defense lawyer, I have a particular perspective on legal issues. I do not pretend to be an impartial judge.
I am a highly partisan advocate for the causes I support.
But as an academic and human rights advocate, my commitment is to the unvarnished truth, impartial justice and the defense of the rights of humans against tyrants.
That’s why I proudly proclaim in the tagline of my website, “Defend human rights. Speak truth to power.”
For the last nine years, I have been speaking truth to users, abusers and misusers power in Ethiopia, in Africa and elsewhere.
To paraphrase George Bush, “I make no distinction between the abusers and misusers of power who commit crimes against humanity in Ethiopia and the hypocrites who harbor and support them.”
I have come to believe that the root of all evil and suffering in the world is ultimately the abuse of political power and the power to abuse political power. Not money.
That is why I will advocate with the same intensity for Syrian refugees suffering under the Assad/ISIL/ISIS regimes as I would for Ethiopians suffering under the T-TPLF.
My concern for human dignity is not tied necessarily to any particular nationality, but to humanity.
As I like to say, it is not about the nationality of the man or the woman but the huMANity of the man and woman.
As most of my readers have known for nearly a decade, I would not have been involved in Ethiopian politics or human rights advocacy but for the Meles Massacres of 2005.

Friday, October 16, 2015

ውሸት ውሎ አድሮ መጋለጡ አይቀርም!!!

October 16, 2015
def-thumbሥልጣንን በጠመንጃ አፈሙዝ ተቆጣጥሮ ያለው የወያኔ አገዛዝ ካለመታከት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ተአምር ሊመስል በሚችል  መንገድ እያሳደኩ ነው እያለ ሲዋሽ አመታት ተቆጥረዋል። በተለይ ምዕራባዊያንን ሲያታልልበት የነበረው የዲሞክራሲ ጭንብል በምርጫ 97 ከተገፈፈበት ወዲህ ላለፉት አስር አመታት ባለ ሁለት አሃዝ እድገት አስመዝግቤያለሁ እያለ እጅ  እጅ እስኪለን ድረስ በባዶ ሜዳ ስለ ልማትና የዕድገት ሲነግረን ሰነበቷል።
ወያኔ በጉልበት በሚያስተዳድራት ኢትዮጵያ የልማትና የእድገት ፕሮፓጋንዳ ስለ ሰበአዊ መብትና ስለዲሞክራሲ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለማፈኛና አፍ ለማዘጊያነት በማገልገል ላይ ይገኛል ። አለማቀፍ የሰባአዊ መብት ተቋማት ስለሰበአዊ መብት ጥሰት ለሚያቀርቡት አቤቱታ ሁሉ የሚሰጠው መልስ “ኢኮኖሚውን እያሳደግን ነው” የሚል ነው። ኢኮኖሚ ማደግ አለማደጉን ትርጉም የሚኖረው ከህዝብ የእለተ ተእለት ኑሮ ጋር ሲያያዝ መሆኑ ሁሉ  ትርጉም አጥቷል። ራበኝ የሚለው ሰው ሁሉ ጠገብኩ ማለቱ ነው ተብሎም ይተረጎማል።
የውሸት ነገር ውሎ አድሮም ቢሆን መጋለጡ አይቀርምና ይኼው በቅርቡ የተከሰተው ድርቅ የወያኔን የውሸት ፕሮፓጋንዳ ክንብንብ ገፎታል። አለም በሙሉ አስር አመት ሙሉ በሁለት አሃዝ ሲያድግ የነበረ ኢኮኖሚ ባለበት ሃገር ውስጥ አንዲት የድርቅ አመት ካለርሃብና ልመና እንዴት መሻገር አቃተው የሚል ጥያቄ በሰፊው በማንሳት ላይ ነው። ወያኔ ለዚህ ጥያቄ መልስ የለውም።  በአለም ዙሪያ ያለው ተመክሮ ሁሉ የሚያሳየው ወያኔ አድጌበታለሁ ብሎ ሲለፍፍ ከኖረው አሃዝ በታች በግማሽ ያደጉ ሃገሮች እንኳ አንድም ጊዜ አንድ የድርቅ ዘመን መሻገር አቅቶአቸው  ሲንገዳገዱና መንግሥታቸው ለልመና ሲሄድ አለመታየቱን ነው።
ኢትዮጵያ ውስጥ ወያኔ የሚያወራውን ያህል ያልሆነ ቢሆንም በአንዳንድ ከተሞች አካባቢ የሚታየው እድገት የተገኘው ከውጭ መንግስታት የገንዘብ ብድር፣ በአለም አቀፍ ተቋማት እርዳታ፣ ስደተኛው ኢትዮጵያዊ በገፍ በሚልከው ገንዘብና ወያኔ ከድሃውና ከነጋዴው ከዝርፊያ ባላነሰ ሁኔታ በሚሰበሰበው ግብርና መዋጮ የተገኘ እንጂ ወያኔ ባስፋፋው ኢንዱስትሪና ልማት እንዲሁም ሀገር ውስጥ በፈጠረው ሀብት አለመሆኑ የሚታወቅ ነው።
የወያኔ ሹማምንትና አገልጋዮች ሀብት በሀብት መሆናቸውን እንደ እድገት ካልቆጠርን በስተቀር  ህዝባችን ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ኑሮውን እንኳን መደጎም አልቻለም ።በዝርፊያ ገንዘብ ሹማምንቱና የወያኔ ባለምዋሎች የገነቡትን ፎቅ የሀገር ልማት ነው ካላልን በስተቀር እውነተኛና የህዝብ ህይወት ከመሰረቱ የሚቀይር ልማት አገር ውስጥ አለመካሄዱ ትንሽ ገለጥ ሲያደርጉት የሚታይ ሃቅ ነው። አንድ የድርቅ ወቅት መሻገር አቅቶት ብዙ ሚሊዮኖችን ከረሃብና እልቂት መታደግ ያልቻለ ኢኮኖሚ አስር አመት ሙሉ በሁለት አሃዝ አድጓል ብሎ የሚያምን ሰው ሊኖር አይችልም።
የወያኔ የኢኮኖሚ አሃዝ “መልከ ጥፉን በስም ይደግፉ” ከሚለው የሀገራችን ግፈኛ አባባል  ብዙም አይለይም። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ለህዝብ በሚጠቅም መንገድ የማደጉ ጉዳይ በመጀመሪያ ፍትሐዊ ኢኮኖሚያዊ ሥርአት መገንባትንና ዴሞክራሲ ማስፈንን ይጠይቃል።
በመሆኑም የዛሬው የወያኔ ኢኮኖሚ የዝርፊያ ኢኮኖሚ እንጂ ህዝባዊ ሽታ የለውም። የኢትዮጵያን ህዝብ እዚህና እዚያ በሚብለጨለጩ ያውም በአብዛኛው በብድርና እርዳታ በተገኙ ልማት ተብዬ ነገሮች ለረዥም ጊዜ ማታለል አይቻልም።
ወያኔ በሚሰጠው አሃዝ የሚያድግ ማንኛውም ሀገር የውጭ ስደተኞችን ያስተናግድ እንደሆን እንጂ ወጣቶች ሞትና ህይወትን አማራጭ አድርገው አይሰደዱበትም። ባለ ሁለት አሃዝ አዳጊ ኢኮኖሚ በየትም ሀገር የስደተኞች ምንጭ ሆኖ ታይቶ አይታወቅም በዘረኛው ወያኔ ተገዢዋ ኢትዮጵያ ካልሆነ በስተቀር።
አርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ትንሳኤ ከዘራፊው የወያኔ ሥርዐት መወገድ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ መሆኑን ያምናል!  ስለዚህም ህዝባችን ወያኔን ለማስወገድ የተጀመረውን ትግል በነቂስ ለመቀላቀል ዛሬውኑ እንዲነሳና ከጎናችን እንዲሰለፍ የማያቋርጥ ጥሪውን ደግሞ ደጋግሞ ያስተላልፋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Wednesday, October 14, 2015

Journalism in Ethiopian Context

October 14, 2015
by Tewedaje Tesfu Biru
Handwritten bulletins which address the daily events of ancient Rome were the earliest journalistic effort made in the first century BC. Then, the first distributed news bulletins appeared in China around 750 AD. Germany, The Netherlands, and England produced newsletters and news books of different sizes in the 16th and 17th centuries.
By the early 18th century, politicians had begun to recognize the enormous potential of newspapers in shaping public opinion. Consequently the journalism of the period was largely political in nature; journalism was considered as an adjunct of politics and each political faction had its own newspaper. It is also during this time struggle for freedom of expression, which is immunity of the communications media including newspapers, books, magazines, radio, and television from government control or censorship, began.press freedom and the fate of journalists in Ethiopia
Ethiopia, in which freedom of expression is guaranteed as the basic right in the constitution, is among the leading countries in the world in suppression of the rights to freedom of expression and access to information. Many private media are banned, and many journalists fled their country and many others thrown to prison only because they criticized the state government. According to Human Rights Watch, Ethiopia is the second country next to Iran in the number of journalists in exile.
Journalism is a socially responsible profession, serving the needs and interest of the society by creating the necessary intelligence they need to lead better lives. However, in Ethiopia most, if not all, government journalists are the watchdogs of the government rather than the public and they are sanctioned by the government to be so. Journalists with strong position to balance their stories would be accused of having conspired with the opposition and are usually labeled as “terrorists” or “anti-government” and taken to prison. In fact, even those who work as watchdogs of the government lead their life in conflict between their professional identity and the situation.
Journalism in Ethiopia is not free of political influence. This can be indicated in the government’s dominance of the media ownership, the appointment of the media managers from the ruling party, and the imposition of restrictive media laws. The government’s clear aim is to ensure that media promote and never criticize government initiatives and policies.
As Human Rights Watch states the Ethiopian government has accused more than 38 journalists with various crimes under the Anti-Terrorism Proclamation since the 2010 election. Journalists who are known to write critical articles face regular and intense pressure from security officials. With the existing degree of censorship, it seems Ethiopia is in the 18th century as far as the development of journalism in the rest of the world is considered. Thus, it can be said that in Ethiopia where freedom of expression is highly suppressed and journalists are in trouble, journalism is fake.
Tewedaj Tesfu Biru, October, 2015, Toronto, Canada

Monday, October 12, 2015

ከመድረክ/ሰማያዊ/መኢአድ ጋር ለመነጋገር እንደሚፈልጉ አቶ ሃይለማሪያም ገለጹ - የሚሊዮኖች ድምጽ

October 12,2015
Millions of voices for freedom - UDJ's photo.
“ከስፖርት ጀምሮ እስከ ሥራ በፓርቲ አባላነት ነው “ ወ/ር ጽጌ ጥበቡ
“ እርስዎ ከምለስ ራ፤እይ ተላቀው ይራስዎት ራእይ መቼ ነው የሚኖሮት ? “ ጥያቄ ለአቶ ኃይለማሮያ
ያለፈው አርብ መስከረም 28 እና ቅዳሜ መስከረም 29 ቀን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ በተገኙበት፣ በአምስቱ አመቱ የእድገትና ትራስንፎርሜሽን እቅድ ዙሪያ፣ ኢሕአዴግ ስብሰባ አድርጓል። በአመስት አመቱ እቅዱ ዙሪያ ከመነጋገር በፊት በሕዝብ የሚነሱ ወቅታዊ የሰብአዊ መብት፣ የፍትህ መጓደልና የብሄራዊ መግብባባት ዙሪያ ዉይይቶች መቅደም አለባቸው በሚል፣ የአራት ደርጅቶች ስብስብ የሆነው መድረክ፣ የሰማያዊ ፓርቲና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ደርጅት (መኢአድ ) ስብሰባዉን አልተሳተፉም።
ከመድረክ ቀጥሎ በ2007 በርካታ ተወዳዳሪዎች በማሰለፍ ሁለተኛ የሆነው ኢዴፓን ፣ ጨመሮ ሌሎች አናሳ ድርጅቶች ስብሰባዉን ተሳትፈዋል። በዶር ጫኔ ከበደ የሚመራው ፣ ኢዴፓ፣ ጥያቄዎችን በማንሳት ጠንካራ ክርክሮች እንዳደረገ ለማረጋገጥ ችለናል። የኢዴፓ ተወካዮች፣ በድፍረትና በግልጽ ያለፈው የአምስት አመት እቅድ እንዳልተሳካ፣ መረጃዎች በማስቀመጥ ለማሳየት የሞከሩ ሲሆን፣ መሰረታዊ የፍትህ የመልካም አስተዳደር፣ የዴሞክራሲ ለዉጦች ተደርገው፣ ሕዝቡን ባቀፈና ባሳተፈ መልኩ ስራ ካልተሰራ፣ መጨው የአምሰት አመት እቅድም አይሳከም ሲሉ ለነ አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ተናግረዋል።
ወ/ሮ ጽጌ ጥበቡ የሚባሉ የኢዴፓ ምክር ቤት አባል፣ “ ከስፐርት ጀመሮ እስከ ሥራ፣ የኢሕአዴግ ፓርቲ አባል ካልተኮነ በቀር ምንም ነገር ማደረግ አይቻልም” ሲሉ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ኢኮኖሚዉን፣ ፖለቲካዉን፣ ሜዲያዉና ሌሎች ሁሉንም ተቋማት ብቻውን እንደሚቆጣጠር በመገልጽ ፣ ተቋማት ገለልተኛ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
“ እርስዎ የመለስን ፎቶ እየያዙ፣ በመለስ ራእይ እያሉ ነው። የራስዎት ራእይ የልዎትም ወይ ? ሲሉ ኤደፓዎች አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በላያቸው ላይ ያለፈው የአቶ መለስ ጥላ ገፈው ፣ ህዝብን አክብረው ፣ “ዴሞክራሲ የሕልዉና ጉዳይ ነው “ ብለው ብዙ ጊዜ የሚናገሩት ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
አቶ ኃይለማሪያም ደርጅታቸው ብዙ ስህተት ያለው፣ ብዙ ነገሮችን ማስተካከል ያለበት እንደሆነ ያመኑ ሲሆን፣ ከተቃዋሚዎች ጋር እየደጋገሙ በመነጋገገር ያሉትን ችግሮች ለመፍታት እንደሚሞክሩም ቃል ገብተዋል።
በስብሰባው ያልተካፈሉ ደርጅቶችም ስብሰባዉ ላለመካፈልል የወሰኑትን ዉሳኔ እንደሚያከብሩ የገለጹት አቶ ኃይለማሪያም፣ በስብሰባው ካልተገኙ ደርጅቶች ጋር ለመወያየትና ለመነጋገር ፍላጎትና ፍቃደኝነቱ እንዳላቸዉም በስብሰባው ወቅት ገልጸዋል።
በኢዴፓና መድድረኩ ላይ በነበሩት በኢሕአዴግ ባለስልጣናት መካከል የጦፈ ክርክርና ምልልሶች የነበብሩ ቢሆንም በሕወሃቱ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ኢቢሲ/ኢቲቪ ግን በስብሰባው የነበረዉን ሁኔታ በግልፅ ለሕዝብ ከማቅረብ፣ እንደ አቶ ትግስቱ አወሉ ያሉትን የሕወሃት አሻንጉሊቶች በማቅረብ፣ የዉሸት ዘገባን ማቅረቡን መርጧል።

Friday, October 9, 2015

የሕወሓት ሰዎች ዶላርን በሰሜን አሜሪካ በ23 ብር እየመነዘሩ ሃብታቸውን በማሸሽ ላይ መሆናቸው ታወቀ

October 10,2015

የሕወሓት ባለስልጣናት ከሃገር ቤት ሃብታቸውን ለማሸሽ እየጠቀሙበት ያለው ዘዴ የኢትዮጵያን ባንኮች ከመጉዳቱም በላይ በሃገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ አስፈሪ ዳመና እንደጣለበት ተሰማ:: በአሁኑ ወቅት የሕወሓትና የተላላኪዎቹ ድርጅቶች ባለስልጣናት በሙስና ያከበቱትን ሃብት እያሸሹ ያሉት እዚህ ሰሜን አሜሪካ ወደ ሃገራቸው ዶላር መላክ የሚፈልጉትን በ23 ብር ሃገር ቤት ላይ እንመነዝርላችኋለን በሚል እንደሚቀበሉና በዚህም ጥቁር ገበያ የሕዝብ ሃብት እየሸሸ መሆኑ ተጋልጧል::

በአሁኑ ወቅት በዋሽንግተን ዲሲ; በሲያትል; በዴንቨር; በሚኒያፖሊስ; በአትላንታ; በዳላስ; በቺካጎ; በሂውስተን; በኦሃዮ; በፖርትላንድ; በላስቬጋስ; በካሊፎርኒያ የተለያዩ ከተሞች; በአሪዞና በተዘረጉ ኔትወርኮች ዶላር በጥቁር ገበያ 23 ብር እየተመነዘረ መሆኑ ታውቋል::

የገንዘቡ ዝውውር የሚደረገው ከላይ በተጠቀሱት ከተሞች ባሉ ኔትዎርኮች መካከል ዶላሩን እዚሁ ይሰጡና ሃገር ቤት በግለሰቦች አማካኝነት በ23 ብር ምንዛሬ ይሰጣል:: ዘ-ሐበሻ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድረገጽ ባገኘችው መረጃ መሰረት በዛሬው ዕለት የዶላር ምንዛሬ ዋጋ 20.85 ሲሆን በ23 ብር በጥቁር ገበያ እየሸጠ ይገኛል::

ዶላር በሕገወጥ መንገድ እንዲህ መተላለፉ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ መንግስት ዘንድ ያለውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት የሚያባብሰው መሆኑ እየታወቀ የሕወሓት ሰዎች እንዴት እንዲህ ባለው ሕገወጥ ተግባር ላይ እንደተሰማሩ የሚያስገርም ነው የሚል አስተያየት የሚሰጡ ሰዎች ከጥቂት ጊዜያት በፊት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ “የኢትዮጵያን መንግስት በኢኮኖሚ ማዳከም ካስፈለገ ከውጭ የሚላኩ ዶላሮች በኢትዮጵያ ባንኮች በኩል መተላለፍ የለባቸውም:: ሕዝቡ ዶላሩ መንግስት እጅ በማይገባበት መልኩ ገንዘቡን ይላክ” ማለታቸውን ይጠቅሳሉ::
ምንጭ ዘ-ሐበሻ

Wednesday, October 7, 2015

በፓርላማው ውስጥ እንቅልፏን የለጠጠችው ወ/ሮ አስቴር አማረ ጋር በእንደርታ ምርጫ ተፎካካሪዋ የነበረው የአረናው አባል ስለሴትየዋ ይናገራል

October 7,2015

ፓርላማው ውስጥ ዛሬ በርካቶች እንደተለመደው እንቅልፋቸውን ሲለጥጡት ውለዋል:: ይህን ተከትሎ የተለያዩ ፎቶዎች ሲለቀቁ ውለዋል:: ከነዚህ እንቅልፋሞች መካከል ደግሞ አንዷ ወ/ሮ አስቴር አማረ ናት:: ከ እንደርታ ትግራይ የመጣችው ይህችው የፓርላማው ተቸካይ ጠርጴዛ ላይ ተቸክላ እንቅልፏን ስትለጥጥ ነበር:: ከ እርሷ ጋር በተፎካካሪነት በአንድ ምርጫ ጣቢያ ቀርቦ በሕገወጡ ምርጫ ተሸንፈሃል የተባለው የአረናው ፓርቲ ተወካይ አቶ ሰናይ የሚከተለውን መልዕክት በፌስቡክ ገጹ አስተላልፏል::

እኝህ እንቅልፋም ወ/ሮ አስቴር አማረ የተባሉት ሴት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የህወሓት የ ወረዳ እንደርታ(መቀለ ዙርያ) ተወካይ ሲሆኑ በ2002 ምርጫ በ ወረዳው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቀረቡት 7 የሚሆኑ የፓለቲካ ፓርቲዎች እኔም ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ሉአላውነት በመወከል ስወዳደር እኔና እሳቸቸው ከባድና እልህ አስጨራሽ ፍኩኩር ያደረግን ቢሆንም ምንም የውድድር ሜዳ፣ገለልተኛ የሆነ የምርጫ ቦርድና ፍትሓዊነት ባልነበረው ምርጫ የህወሓት ካድሬዎች 1ለ 5 በማደራጀት ያለና የሌለ አቅማቸው የሀይልም ጭምር በመጠቀም እዚ ግባ በማይባልልና በተጭበረበረ ምርጫ ፓርላማ ሊገቡ ችለዋል።

በጣም እሚገርመው ነገር ወይዘሮ አስቴር አማረ የተመረጡበት ወረዳ ያልተወለዱበት፣ያላደጉበትና የማያውቁት መሆኑ ነው።ፓርላማ ገብተው መተኛታቸውም ለመረጣቸው ህዝብ ንቀት መግለጫ ዋነኛ ምስክር ነው።በአሁኑ ግዜ እኔ በፓለቲካ ልዩነቴ ምክንያት በደረሱብኝ ችግሮች ከምወዳት አገሬና ከምወደው ወገኔን ርቄ በስደት ስንከራተት እንቅልፋምዋ ግን ደልታት ፓርላማ ውስጥ ላሽ ብላለች።

senay amare
ወይ አገሬ

Tuesday, October 6, 2015

ዘራፊው ሕወሓት ቁልፍ ቦታዎችን በመያዝ ውሳኔ ሰጪ ያልሆኑ ወንበሮችን ለአሽከሮቹ አድሏል::

October 6,2015
- አቶ ሬድዋን ሁሴን በሃስት ሲምሉለት የነበረውን ወንበር አጥተዋል::
- ሃይለማርያም ከኒውዮርክ መልስ ሁለት ቀን ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ ከሰው እንዳይገናኙ ተደርገዋል::
- ጥያቄ የሚያበዙት አቶ አለማየሁ ተገኑ እና አቶ ሶፊያን አህመድ ከአሽከርነት ቦታቸው ተነስተዋል::
- ትግላችን ላይ በማተኮር ሕወሓትን ከነአሽከሮቹ ልናጠፋቸው ይገባል::
Hailemariam
 ምንሊክ ሳልሳዊ:- የሕወሓት አሻንጉሊት የሆነው ሃይለማርያም ደሳለኝ በዛሬው እለት ባቀረበው የቸብ ቸብ ካቢኔ መሰረት ሕወሓት የጦር ሃይሉን የውጪ ጉዳዩን የደህንነቱን የኮሚኒኬሽን እና አስፈላጊ ቀልፍ ጉዳዮችን በመቆጣጠር ውሳኔ ሰጪ የማይባሉ ተራ ቦታዎችን ለአሽከሮቹ በማደል የተዋቀረ ሲሆን አለማየሁ ተገኑ እና ሶፍያን አህመድ ምን እንደዋጣቸው አይታወቅም::ከኒውዮርክ ስብሰባ መልስ ሁለት ቀን ከመኖሪያ ቤቱ እንዳይወጣ እና ከሰው እንዳይገናኝ የታገደው ሃይለማርያም ደሳለኝ ራሱን ፈልጎ አለማግኘቱ እና በአሽከርነት መኖሩን ቤተሰቦቹን እያበሳጨ መሆኑ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ይናገራሉ::
ቁልፍ የሆኑ ስልጣኖቹን የተቆጣጠረው እና በዘመድ አዝማድ ተሞልቶ በከፍተኛ የሃገር እና ሕዝብ ሃብት ዘረፋ ላይ የተሰማራው ሕወሓት ባለፈው የኢሕአዲግ ስብሰባ ወቅት አንዳንድ አመራሮቹ ያነሱትን ጥያቄ ተከትሎ ከስልጣን እንደሚባረሩ ሲነገር ነበር:: የወያኔና አሽከሮቹ ሹመት እንደሚከተለው ነው:-
አቶ ደመቀ መኮንን – ም/ጠቅላይ ሚኒስትር እና የማህበራዊ ዘርፍ ክላስተር አስተባባሪ
ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል –በም/ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
ወይዘሮ አስቴር ማሞ – በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ እና የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ ሲራጅ ፈጌሳ – የመከላከያ ሚኒስትር
ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም – የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
አቶ ካሳ ተክለብርሃን – የፌደራል ጉዳዮችና አርብቶ አደር አካባቢ ልማት ሚኒስትር
አቶ ጌታቸው አምባዬ – የፍትህ ሚኒስትር
አቶ አብዱላዚዝ መሀመድ – የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር
አቶ ተፈራ ደርበው – የእርሻ እና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ ስለሺ ጌታሁን – የእንሰሳትና የዓሳ ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ አህመድ አብተው – የኢንዱስትሪ ሚኒስትር
አቶ ያዕቆብ ያላ – የንግድ ሚኒስትር
አቶ አብይ አህመድ – የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
አቶ ወርቅነህ ገበየሁ – የትራንስፖርት ሚኒስትር
አቶ ሙኩሪያ ሀይሌ – የከተማ ልማት እና ቤቶች ሚኒስትር
ዶክተር አምባቸው መኮንን – የኮንስትራክሽን ሚኒስትር
አቶ ሞቱማ መቃሳ – የውሃ፣ መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስትር
አቶ ሽፈራው ሽጉጤ – የትምህርት ሚኒስትር
አቶ ቶሎሳ ሻጊ – የማዕድን፣ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስትር
ዶክተር ከሰተብርሀን አድማሱ – የጤና ጥበቃ ሚኒስትር
አቶ አብዱልፈታህ አብዱላሂ – የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር
ኢንጂነር አይሻ መሀመድ – የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር
ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ -የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ሚኒስትር
ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም – የአካባቢ ደን ልማት እና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር
አቶ ሬድዋን ሁሴን – የወጣቶች እና ስፖርት ሚኒስትር
ወይዘሮ ደሚቱ ሀምቢሳ – የመንግስት የልማት ድርጅቶች ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።
አቶ በከር ሻሌ – የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬከተር
አቶ ጌታቸው ረዳ – የመንግስት ኮሙዩንኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሀላፊ ሚኒስትር
አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ – የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር
ዶክተር ይናገር ደሴ – የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር
ትግላችን ላይ በማተኮር ሕወሓትን ከነአሽከሮቹ ልናጠፋቸው ይገባል::በአንድነት በመቆም ሃገራችንን ከጅቦች እናድናት:

Sunday, October 4, 2015

ድርጅታችንን እናጠንክር፤ በጽናት እንታገል!

October 4, 2015
def-thumb“የአርበኞች ግንቦት 7 አባል በመሆኔ እኮራለሁ” እያሉ በአገዛዙ የይስሙላ ችሎት ሳይቀር በድፍረት የሚናገሩ ወጣቶች ተፈጥረዋል። ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለዲሞክራሲ፣ ለእኩልነትና ለሀገር አንድነት መስዋዕትነት መክፈል የሚያኮራ ተግባር መሆኑ በተግባር የሚያሳዩ ወጣቶች መጥተዋል፤ አሁን በርካቶችም እየመጡ ነው። ወያኔ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በማኅበረሰባችን ውስጥ የዘራው የፍርሀትና የአድርባይነት ስሜት በራሱ በወያኔ የአገዛዝ ዘመን ተወልደው ባደጉ ወጣቶች እየተናደ፤ በምትኩ ሊጠፋ ተቃርቦ የነበረው የአገር ፍቅርና የአርበኝነት ስሜት እያንሰራራ ነው።
ቅንነት፣ ሀቀኝነት እና ጽናት ከተጣሉበት ጉድጓድ አቧራቸውን አራግፈው እየተነሱ ነው። በማኅበረሰባች ውስጥ ትልቅ የስነልቦና አብዮት እየተካሄደ ነው።
ከስነልቦና ለውጡ ጋርም በተግባር የአገር አድን ሠራዊትን የመቀላቀል ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች ቁጥር በከፍተኛ መጠን እየጨመረ ነው። ወጣቶች የአገራቸው ባለቤት መሆናቸው ተገንዝበው የፓለቲካ ሥርዓት ለውጥ ለማምጣት በቁርጠኝነት መነሳታቸው ተስፋ ሰጪ ነገር ነው።
አርበኞች ግንቦት 7 በዚህ የለውጥ ወቅት ውስጥ ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ አጽንዖት ልንሰጣቸው ስለሚገቡ የድርጅትና የሥነሥርዓት (ዲሲፕሊን) አስፈላጊነት ላይ የጋራ ግንዛቤ መያዝና በተግባርም መተርጎም አስፈላጊ ነው ብሎ ያምናል።
ወጣቶች ትግሉን ለመቀላቀል መሻታቸው መልካም ነገር ነው። ሆኖም ግን በድንገት ብድግ ብለው መንገድ ከመጀመር ይልቅ ከሚያምኗቸው ወዳጆቻቸው ጋር የመሠረቱት፤ ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋርም ትስስር የፈጠረ ስብስብ አካል ሆነው መቆየታቸው እጅግ አስፈላጊ ነው።
በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ሆኖ የሚስጢር ድርጅት ማዋቀር አስቸጋሪ መሆኑ የማያጠራጥር ቢሆንም የማይቻል ነገር ግን አይደለም። ወጣቶቻችን በአምባገነን ሥርዓት ውስጥም ሆነው በዲሲፕሊን የታነፀ ድርጅት የመፍጠርን ክህሎት መላበስ ይገባቸዋል። ይህንን ማድረግ ስንችል ነው የህወሓትን ፀረ-አገርና ፀረ-ትውልድ ተግባር ማክሸፍ የምንችለው። ትግሉን በሁሉም የኢትዮጵያ ግዛቶች ማቀጣጠል የምንችለው በየአካባቢው የተደራጀ የለውጥ ኃይል ሲኖረን ነው። ስለሆነም የምስጢር የተደራጀ አካል በየመኖሪያና የሥራ አካባቢዎቻችን ሁሉ እንዲኖር ማድረግ ከአጣዳፊ ሥራዎቻችን አንዱ እናድርገው።
ሁለተኛው ነጥብ ሥነሥርዓትን የሚመለከት ነው። ሥነሥርዓት ከሌለ ድርጅት የለም። የህወሓት አገዛዝ ያሳደረብን ጎጂ የባህል ተጽዕኖ ከባድ በመሆኑ ራሳችንን በሥነሥርዓት ለማነጽ መልፋት ይጠበቅብናል። አገራችንና ራሳችንን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ አውጥተን የተሻለ ሥርዓት ማምጣት የምንችለው ራሳችን፣ ድርጅታችን እና ተግባሮቻችን ለሥነሥርዓት ተገዢ ስናደርግ ነው። የነፃነት ታጋዮች ራሳቸውን ለሥነ ሥርዓት ያስገዙ መሆን ይኖርባቸዋል። አስተሳሰባችን ራሱ ሥነ ሥርዓት የያዘ ሊሆን ይገባዋል። እንደዚሁም ሁሉ ተግባሮቻችን በሥነሥርዓት የታነጹ ሊሆኑ ይገባል።
የንቅናቄዓችንን መዋቅር በመላው አገራችን ከዘረጋን፤ ራሳችንን፣ አስተሳሰቦቻችንና ተግባሮቻችን በሥነሥርዓት ከመራን፤ ቅንነት፣ ሀቀኝነትና ጽናት ከተላበስን ድላችን ቅርብ እና አስተማማኝ ነው። ለውጥን የሚናፍቅ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከላይ የተጠቀሱትን ተግባራት ይተግብር።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Thursday, October 1, 2015

ከመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የስንብት ጥያቄ የሚያቀርቡ መኮንኖች ቁጥር እያሻቀበ ነው

October 1,2015
መቶ በመቶ ለማለት በሚያስደፍር ሁኔታ ከአንድ አካባቢ በወጡ የህወሓት አባላት ድኩማን ወታደራዊ አዛዦች ብቻ ቁጥጥር ስር ሆኖ በከፋ አስተዳደራዊ በደል እየማቀቀ በዘር ሸለቆ ውስጥ የሚገኘው ብዙኃኑ የመከላከያ ሰራዊት የሰባት ዓመታት አገልግሎት የኮንትራት ጊዜውን የጨረሰው የስንብት ጥያቄ ያዘሉ ደብዳቤዎችን ያለማቋረጥ እያስገባ በየእርከኑ የሚገኙ የመከላከያ የአስተዳደር ቢሮዎች በማመልከቻ ማዕበል ክፉኛ እየተመቱ የሚገኙ ሲሆን የአገልግሎት ጊዜው አልሞላ ብሎት የስንብት ደብዳቤ ማስገባት ያልቻለው የሰራዊቱ አባል ደግሞ የሰቀቀን ኑሮውን ለማሳጠር በራሱ እርምጃ እየወሰደ ያለምንም ፋታ እየከዳ ነው ሲል የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ዘግቧል::
(Photo File)
(Photo File)















ድኩማኖቹ ህወሓታዊያን የመከላከያ ሰራዊቱ አዛዦች የአገልግሎት ጊዜ ኮንትራታቸውን ጨርሰው የስንብት ደብዳቤ ለሚያስገቡት በስርዓቱ የተንገሸገሹ እና በእጅጉ ተማረው ተስፋ የቆረጡ ስፍር ቁጥር የሌላቸው የሰራዊቱ አባላት “ከመከላከያ ሰራዊቱ ፈፅሞ መልቀቅ አይቻልም…” የሚል አሉታዊና ድፍን ያለ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
በተጨማሪም ድኩማኖቹ ወታደራዊ አዛዦች የአገልግሎት ዘመኑን የጨረሰ ማንኛውም የመከላከያ ሰራዊት አባል በአሁኑ ሰዓት የስንብት ጥያቄ የማቅረብ መብት እንደሌለውና አሰናብቱኝ ብሎ በሚያመለክት ላይ እርምጃ የሚወስዱ መሆናቸውን ጠንከር ያለ መመሪያ አስተላልፈዋል፡፡
ከየማሰልጠኛው ተመርቀው በየጊዜው ሰራዊቱን የሚቀላቀሉ አዳዲስ አባላት ብዙም ሳይቆዩ ስለሚከዱ “ነባሩ ሰራዊት” ከተሰናበተ በእነሱ ላይ ቅንጣት ታክል እምነት ስለሌላቸው በአገዛዙ ላይ የከፋ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል በማብራራት በማሳመን ለማባበል እየሞከሩ ይገኛሉ፡፡
የህወሓት አገዛዝ በየጊዜው ከመከላከያ ሰራዊቱ የሚከዱትን አባላት ከየተሸሸጉበት አድኖ የመያዝ ሰፊ እንቅስቃሴ አድርጎ ሳይሳካለት ቀርቷል፡፡
በየጊዜው ያለምንም ፋታ የሚከዱ የሰራዊቱ አባላት ወደየ ትውልድ ቀያቸው አይደለም የሚመለሱት፤ ገሚሶቹ ከነትጥቃቸው በረሃ ወርደው ይሸፍታሉ፤ አብዛኞቹ የነፃነት ትግሉን ይቀላቀላሉ፤ ቀሪዎቹ ደግሞ ድምበር ተሻግረው እግራቸው ወደመራቸው ይሰደዳሉ፡፡
በአጠቃላይ አሁን እጅግ በጣም በርካታ አባላት ላነሱት የስንብት ጥያቄ የተሰጠውን “አይቻልም” የሚል ድኩማን ህወሓታዊ ወታደራዊ አዛዦች ምላሽ ተከትሎ በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ ከዳር እስከ ዳር ሰፍኖ የቆየውን ውጥረትና አለመተማመን ከጫፍ አድርሶት አገዛዙ ሊቆጣጠረው ከሚችለው በላይ የሆነ ከባድ አደጋ እያንዣበበ ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን በጄኔቭ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ካለው 30ኛ ጉባኤ ስብሰባ ረግጠው ወጡ

October 1,2015
All members with the exception of Russia's UN Ambassador Vitaly Churkin and China's deputy U.N. Ambassador Wang Min vote in the United Nations Security Council in favor of referring the Syrian crisis to the International Criminal Court for investigation of possible war crimes at the U.N. headquarters in New York May 22, 2014. REUTERS/Lucas Jackson (UNITED STATES - Tags: POLITICS) - RTR3QEAZ
ተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን በጄኔቭ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ካለው 30ኛ ጉባኤ ጋር ተያይዞ በተጠራ መድረክ ላይ የተጋበዙት የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን ስብሰባ ረግጠው ወጡ። ስኞ እለት የኢትዮጵያን ሰብዓዊ መብት በተመለከተ በተጠራው ስብሰባ ላይ የተገኙትና በኋላ በቀረበው ሪፖርት ሳይደሰቱ ስብሰባውን ረግጠው የወጡት የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን ወደ ስብሰባው አልተመለሱም። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተወካዮች ጨምሮ የተለያዩ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችና ግለሰቦች በጄኔቭ ስዊዘርላንድ በመገኘት በወቅታዊ የኢትዮጵያ የሰብኣዊ መብት አያያዞች ዙሪያ መወያየታቸውን እማኞች አስታውቀዋል። ይሁንና የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች በመድረኩ ሊነሱ በሚችሉ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ዙሪያ ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ሲጠበቅ፣ ከጉባኤው ረግጠው መውጣታቸው ታውቋል።

ሂውማን ራይትስ ዎችን ጨምሮ በርካታ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በኢትዮጵያ ያለው የሰብዓዊ መብት ረገጣና አፈና ተባብሶ መቀጠሉን ገልፀዋል። ሁሉንም የፓርላማ ወንበሮች በብቸኝነት ተቆጣጥሮ የሚገኘው ገዢው የኢህአዴግ መንግስት፣ የዜጎችን ሃሳብን የመግለጽ መብት ከማስፋፋቱ በተጨማሪ በነጻ የመገናኛ ብዙሃን ላይ የሚወስደው እርምጃ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ድርጅቱ አመልክቷል። ከትናንት በስቲያ ሰኞ የተካሄደውን የሰብዓዊ መብት መድረክ ያዘጋጀው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብኣዊ መብት ኮሚሽን በተለያዩ ጊዜያት በኢትዮጵያ ስላለው የሰብኣዊ መብት አያያዝ ስጋቶችን ሲገልፅ መቆየቱ ይታወሳል። በጄኔብ በተካሄደው በዚሁ ልዩ መድረክ የተሳተፉ በርካታ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ወቅታዊ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ዙሪያ ረፖርት ማቅረባቸውንም በመድረኩ የተሳተፉ አካላት ገልፅዋል።
የእንግሊዝ የፓርላማ አባላትን ጨምሮ በርካታ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጀቶች ኮሚሽኑ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አያያዝን ጨምሮ በተለያዩ የፖለቲካ እስረኞች ላይ ክትትልን እንዲያደርግ ጥያቄ አቅርበው እንደሚገኙም ተችሏል። የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች መድረኩን ረግጠው ስለወጡበት ምክንያት የሰጡት ምላሽ የለም።