Thursday, April 3, 2014

በእጅ አዙር የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መግስት ስለባ የሆነው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ለወግኖቹ ክበር እስከ መስወአትነት እንደሚቆም ከስርቤት አረጋገጠ !

April2/2014

በእጅ አዙር የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መግስት ስለባ የሆነው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ለወግኖቹ ክበር እስከ መስወአትነት እንደሚቆም ከስርቤት አረጋገጠ !
ባልታወቀ ምንክንያት ክቀርብ ግዜህ ወዲህ በሳውዲ ጸጥታ ሃይሎች ለእስር የተዳረገው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በወገኖቹ ላይ የሚፈጸመውን በደል እይተከታተለ ለሚዲያ የሚያበቃ በአረቡ አለም የሚገኝ ብቸኛ ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ ነው ። ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ለወህኒ ከመዳረጉ በፊት ባለፉት አመታት በወገኖቹ ላይ የሚደርስውን ግፍ እና በደል አስመለክቶ ያቀርብ በነበረው የማለዳ ወግ መረጃ ቅበላው ያልተደሱቱ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ሹማምንቶች እና በወገኖቻቸው ህይወት ዶላር ሲሰበስቡ በከረሙ አፋኞች ማስፈራያ ይደርሰበት እነደበር ለማወቅ ተችሏል ።

 ጀግናው ጋዜጠኛ ለነዚህ ወሮበሎች ሳይበረከ እስከመጨረሻው ለወገኑ ክበር የህይወት መስወአትነት ለመክፈል የግባውን ቃልኪዳን ጠብቆ በእሳት ተፈትኖል። ዛሬ በዚህ ጀግና ጋዜጠኛ ላይ የተፈጸመውን ደባ እና ከጀርባው እና ማን እንዳሉ በስፋት መግለጽ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ነጻ ለማውጣት ለወህኒ ከተዳረገበት ግዜ ጀምሮ እሳካሁን እተደረገ ያለውን ጥረት ስለሚያወሳስበው ወደ ዝርዝር ሃስቡ ከመግባት መቆጠብ ግድ ብሏል ። ይህን ታላቅ ጋዜጠኛ ከተቻለ ከሳውዲ አረቢያ እንዲባረር አሊያም ወህኒ እንዲማቅቅ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ያለፈጸመውን ፈጸመ በሚል የጥላቻ ዘመቻ ከፌስ ቡክ አንስተው ለሳውዲ ጸጥታ ሃይሎች የተሳሳተ መረጃ እስከመስጠት የድረሱ ዛሬም ዛሬም እንቅልፍ አጥተው የሚያማትሩ የህዝብ ጠላቶችን የሃሰት ውንጀላ በመከላለከል ይህን ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ ከደረሰበት አደጋ ልንታደገው ይገባል። 
Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ

No comments: