Friday, April 11, 2014

የገመና ድራማው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ የፍርድ ቤት ማዘዣ ደረሰው (ማዘዣውን ይዘናል)

April 11/2014

 በከሳሽ የፊልም አሰሪ ወ/ሮ ቤተልሄም አበበ እና በተከሳሽ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ይተላለፍ በነበረው ገመና ድራማ የዶ/ር ምስክርን ገፀ ባህርይ ወክሎ የተወነውና በተለያዩ ፊልሞች ላይ የተወነው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ መካከል ያለው የፍርድ ሂደት መታየቱን ቀጥሎ አርቲስቱ የፍርድ ቤት ማዘዣ እንደደረሰው ለዘ-ሐበሻ እስከነ ማስረጃው የደረሰው መረጃ አመለከተ።

ከዚህ በፊት በዚሁ ክስ የተነሳ በካራማራ አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ የተለቀቀው አርቲስት ዳንኤል በወ/ሮ ቤተልሄም የቀረበበት አቤቱታ ለፊልም ሥራ 662 ሺህ 120 ብር ከተቀበለ በኋላ ፊልሙን ሳይሰራ ቀርቷል በሚል “የማጭበርበር” ክስ እንደሆነ ተገልጿል።

ከሳሽ ወ/ሮ ቤተልሄም አበበ የካቲት 6 ቀን 2006 ዓ.ም ጽፋ ለፍርድ ቤቱ ያቀረበችው ባለ 5 ገጽ የክስ ማመልከቻ፣ 2 ገጽ የማስረጃ ዝርዝር፣ 2 ገጽ ልዩ ልዩ ማስረጃዎች በድምሩ 9 ገጽ ክሱን የሚያስረዱ ወረቀቶች ከፍርድ ቤት ማዘዣ ጋር ለአርቲስት ዳንኤል የደረሰው ሲሆን አርቲስቱም መጋቢት 22 ቀን 2006 ዓ.ም በጠበቃው በኩል መረከቡን በፊርማ አረጋግጧል።

በዚህም መሠረት ዳንኤል ለቀረበበት ክስ ሚያዝያ 3 ቀን 2006 ዓ.ም ለከፍተኛው ፍርድ ቤት በሬጅስራር ጽህፈት ቤት በኩል ማስረጃውን እንዲያቀርብና እንዲሁም ግንቦት 12 ቀን 2006 ዓ.ም ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ጉዳዩ በችሎት እንዲታይ ፍርድ ቤቱ አዟል።
ዘ-ሐበሻ ይህን ጉዳይ ተከታትላ ትዘግባለች።


ዘ-ሐበሻ

No comments: