Wednesday, April 9, 2014

የኢህአዴግ ‘መንግስት’ ጭካኔ….እሰከ ብልት መግረፍ….

April 9/2014
ሼኽ መከተ ሙሄ ይባላሉ፡፡ የ47 አመት ጎልማሳ ሲሆኑ በጣም የተከበሩ የሀይማኖት ሰው ናቸው፡፡ በጥር 2004 የቋቋመው እና የ 3ቱን የህዝበ ሙስሊሙን ጥያቄዎች ይዞ ሲንቀሳቀስ በነበረው የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል የነበሩ በመሆናቸውና በህጋዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድም ለመንግስት የመብት ጥያቄ በማቅረባቸው አሸባሪ ተብለው ከተያዙበት ሐምሌ 2004 ጀምሮ በማእከላዊ እና ቂሊንጦ ለብዙ ግፍ እና ስቃይ ተዳርገዋል፡፡
ዛሬ በዋለው ችሎት መከላከያ ቃለቸውን ያቀረቡት የቀድሞው የሸሪዓ ፍርድቤት ፕሬዝደንት ሼኽ መከተ ሙሄ በማእከላዊ የደረሰባቸውን አሰቃቂ ስቃይ (የቶርቸር ምርመራ) አጋልጠዋል፡፡ ራሳቸውን መርማሪ ብለው በሚጠሩ ግለሰቦች ለተከታታይ ድብደባ መዳረጋቸውን፣ራቁታቸውን በማድረግና ብልታቸውን በመግረፍ በራሳቸውና በጓዶቻቸው ላይ በግድ እንዲመሰክሩ የተፈፀመባቸውን ዘግናኝ ስቃይ ዘርዝረው አስረድተዋል፡፡
"ነሀሴ 5 2004 ከፍተኛ የሆነ እንግልትደርሶብኛል በዕለቱ አንድ መርማሪወደኔ በመምጣት አይኔን በጨርቅከሸፈነ በሀላ ይዞኝ ከታሰርኩበትበማስወጣት ብዙ ደረጃ እያስወጣናእያስወረደ ወደ አንድ ክፍል ካስገባኝበሀላ ፊቴ ላይ የነበረውን ጨርቅበመፍታት በመርማሪ ተክላይ መሪነትሙሉ ልብሴን በማስወለቅ 2,000ቁጭ ብድግ ስራ ብለውኝ በመስራትላይ እያለሁ ከፍተኛ ድካም ደክሞኝተዝለፍልፌ በምወድቅበት ሰዓትጉልበቴን መቆም እስኪያቅተኝበመግረፍ ያሰቃዩኝ ሲሆን ከዛምበመቀጠል ብልቴን በተለያዩ መንገዶችበመጉዳት ሲያሰቃዩኝ ከቆዩ በሀላእራሴን ስቼ ወድቄ የነበረ ሲሆንመርማሪዎቹም ውሀ በማምጣትሲደፉብኝ የነቃሁ ሲሆን በማስከተልምውሀ ውስጥ በመዘፍዘፍ ከፍተኛእንግልት ካደረሱብኝ በሀላ አይኔንበድጋሚ በጨርቅ በማሰር አንድ ሰውወደተወሰነ ቦታ ከወሰደኝ በሀላ ጥሎኝየሄደ ሲሆን መቆም ስላቃተኝግድግዳውን ተደግፌ በቆምኩበት ሰዓትአንድ የማረሜያ ቤቱ ፓሊስ ወደኔበመምጣት ምን ትሰራለህ እዚህ?ለምንስ አይንህን አሰርክ በሚለኝ ሰዓትማን እዚህ ቦታ እንዳመጣኝእንደማላውቅና አይኔን እንዳሰሩኝነግሬው ፍታውና ከዚህ ሂድ በሚለኝሰዓት መፍታት አቅሙ እንደሌለኝስነግረው እሱ አይኔን ፈቶልኝወዳመጡኝ ክፍል በመውሰድ የጣሉኝሲሆን እዛ ጥለውኝ በሚሄዱ ሰዓትማንም አጠገቤ ባለመኖሩና ቁስሌንእንኳን በቫዝሊን ሚያሽልኝ ሰውበማጣቴ ከፍተኛ ሀዘንና ጉዳትደርሶብኛል..."ሼኽ መከተ ሙሄ ይባላሉ፡፡ የ47 አመትጎልማሳ ሲሆኑ በጣም የተከበሩየሀይማኖት ሰው ናቸው፡፡ 
በጥር 2004የቋቋመው እና የ 3ቱን የህዝበሙስሊሙን ጥያቄዎች ይዞ ሲንቀሳቀስበነበረው የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴአባል የነበበሩ በመሆናቸውና በህጋዊናሰላማዊ በሆነ መንገድም ለመንግስትየመብት ጥያቄ በማቅረባቸው አሸባሪተብለው ከተያዙበት ሐምሌ 2004ጀምሮ በማእከላዊ እና ቂሊንጦ ለብዙግፍ እና ስቃይ ተዳርገዋል፡፡ዛሬ በዋለው ችሎት መከላከያቃለቸውን ያቀረቡት የቀድሞው የሸሪዓፍርድቤት ፕሬዝደንት ሼኽ መከተ ሙሄበማእከላዊ የደረሰባቸውን አሰቃቂስቃይ (የቶርቸር ምርመራ)አጋልጠዋል፡፡
ፍትህ ከአላህ እነጂ ከሌላ አንጠብቅም!

No comments: