Wednesday, August 13, 2014

በምእራብ ኢትዮጵያ ለኩምሩክ ድንበር አቅራቢያ ጦርነት ተካሄደ።

August 13/2013

ከወያኔያዊ ምርጫ በፊት የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ሊያሰጋ ይችላል ሲሉ ዲፕሎማቶች ተናግረዋል።

ምንሊክ ሳልሳዊ
ወያኔ ራሱን ለማንገስ ከሚጠራው ምርጫ በፊት በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ድንበር አከባቢዎች ጦርነት ሊካሄድ ይችላል ሲሉ በኢትዮጵያ የሚኖሩ ዲፕሎማቶች ተናግረዋል።በተለያዩ አጋጣሚዎች የተነሱ የሳተላይት ፍቶዎች በማስረጃነት በመጥቀስ ይህን ሰሞን በአዲስ አበባ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ከአፍሪካ ህብረት ሰዎች እና ከአከባቢው የፖለቲካ አዋቂዎች ጋር የተለያዩ ስብሰባዎችን የሚያካሂዱት ዋናው የዚሁ ጦርነት ስጋትና አከባቢው ላይ ብሄራዊ ጥቅማቸው ላይ ምን ሊከሰት ይችላል የሚለውን በመገምገም ላይ መሆናቸው ታውቋል።

ዲፕሎማቶቹ የአሜሪካ መንግስት የሲአይኤን ሪፖርት ተከትሎ በትራንስፖርት ቢሮአቸው አማካኝነት በሰሜን ኢትዮጵያ የአየር በረራ የሚከለክል ደንብ ማስተላለፉ ይታወቃል፡፤ የዚህ ጉዳይ ዋነኛ ምክንያት ደሞ አከባቢው ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ መሆኑና በጦርነት ቀጠና የተመዘግበ ድንገት ጦርነት ይነሳል የሚል ግምት የተወሰደበት መሆኑ በአከባቢው ከፍተኛ የሆነ ከባድ መሳሪያዎች ታንኮች እና ብረት ለበስ አውዳሚ የጦር መሳሪያዎች የተከማቹ በመሆኑ ጦርነት አይቀሬ ስለሆነ በቋፍ ላይ ባለ የጦርነት ቀጠና ላይ አየር ማብረሩ ስጋት እንደሆነ ይናገራሉ፡፤ስለዚህ እንደ ዲፕሎማቶቹ እምነት ከወያኔያዊው ምርጫ በፊት የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ያስጋል።

በምእራብ ኢትዮጵያ በቤንሻንጉል ጉምዝ ወደ ድንበር ከተማው ኩምሩክ አክባቢ በግምት 50 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው የወያኔው መከላከያ ሰራዊት ካምፕ አቅራቢያ በሰራዊቱ እና ከደቡብ ሱዳን ሰርገው ገብተዋል በሚባሉ ሃይሎች መካከል የ3 ሰአታት ጦርነት መካሄዱን አንድ የምእራብ እዝ መኮንን በላኩልኝ መረጃ ገልጸዋል።

ወታደሮቹ በክምፑ አከባቢ ቅኝት በሚያደርጉበት ጊዜ ድንገት የመጡ ሰርጎቦች የተባሉ ሃይሎች አከባቢውን በመውረር ከባድ ጉዳት ያደረሱ ሲሆን 26 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ሲግደሉ በርካቶች ቆስለዋል። በዚህ የሰአታት ጦርነት እንደ መኮንኑ አባባል ከተዋጊዎቹ ወገን ጥልው የሸሹት ሁለት ሬሳ ብቻ ነው ብለዋል።

No comments: