Friday, August 4, 2017

(ሰበር ዜና ፓርላማ) ያለመከሰስ መብታቸው በፓርላማ የተነሳው የገንዘብ እና የኢኮኖሚ ትብብር ሚንስትር ዴኤታ በፖሊስ ቁጥጥር ዋሉ

Augest 4,2017
በሙስና ወንጀል ጠረጠርናቸው የሚሉአቸውን ባለስልጣናት እና ነጋዴ ማህበረሰብን ማደን ከተያዘ ሦስተኛ ሳምንቱን መያዙ የተገለፀ ነው ። በአሁን ሰአት የህወሀት መንግስት ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ነው በተባለበት በዚህ ጊዜ ፣በስሩ የነበሩትን የከፈተኛ ባለሥልጣን አመራሮችን ከቦታቸው አንስቶአል ፣ የድርጅቱ ሚስጥር ጠባቂ ተብለው በሙስና ውስጥ የተዘፈቁትን በአምባሳደርነት ሹመት ወደ ተለያዩ ቦታዎች አሸጋሽጎአቸዋል።
ሆኖም ግን በመንግስት እና በውጭ አገራት የተመሰረቱ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን የሙስና መንሰራፋት መንግስት በይፋ እያወቀ  በሌሎች ትንንሽ ገዳዮ ላይ ትኩረቱን መጣሉ የሃገሪቱን ደህነንት የማይፈልግ መንግስት መሆኑን ያሳያል ሲሉ አንድ የመንግስቱ ባለስልጣን ለማለዳ ታይምስ የፃፉት ደብዳቤ ይገልጣል ።
በተለይም ይላሉ እኝሁ ባለስልጣን በዩኤስ አይድ እና በህወሃት መንግስት ባለስልጣን የተካሄደው ስምምነት የሀገሪቱን ውስጣዊ ደህንነት አሳልፎ የሚሰጥ በመሆኑ የተነሳ የሀገርና የአካባቢ ጥበቃ ተብሎ የተመደበውን ገንዘብ ቢመለስም ሆነ ይህነኑ ጉዳይ ለማስፈፀም ተብሎ ከውጭ ጉዳይ መስሪያቤት ዋና ሚንስትር ጀምሮ እስከ ጠቅላይ ምንስትር መስሪያ ቤቱ ድርስ የዩኤስ ኤይድ ድርጅት ለስራ ማስሌጃቸው ይሆን ዘንድ ለሚንስትሮቹ በግላቸው  የሰጠውን ገንዝብ እንዲመረምር እና ሚንስትሮችም ከፍተኛውን ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል ሲሉ ጠቁመዋል ።
ሀገሪቱን የውስጥ ችግሮቿን እያዩ ችግር ፈጣሪ አካላትን በበጎ አድራጎት በኩል መፍቀድ አሳፋሪ ቢሆንም ፣በአሁን ሰአት ሀገሪቱን ለማፍረስ እና የእር በእርስ ግጭት ለመቀስቀስ ቀላል እንደሆነ በደንብ አጥንተውበት ስር የሰደደ ሂደት ውስጥ መሆናቸውን እና በየክልሉ የአካባቢ ጥበቃ ተብሎ የተመሰረተው ይህንን አሜሪካ ድርጅት ጥናት በአስቸኳይ መንግስት ስራውን ማስቆም አለበት አለበለዚያ ግን ህዝቡን ለማጫረስ በዝግጅት ላይ መሆኑን ያመላክታል በማለት ስጋታቸውን ገልፀዋል።
ይሄው የአሜሪካ ድርጅት የኢትዮጵያ ችግሮች የቱ ጋር እንደሆነ የትኛው ቦታ ላይ የብሄሮች ግጭት እንዳለ ፣መንግስት ከየትኛው ማህበረሰብ ጋር አየተፋለመ እንዳለ ጠንቅቆ በጥናቱ ላይ ያወቀው ሲሆን ካለበት መንበረ ስልጣን ለማውረድም ይሁን ህዝቡን እርስ በእር ለማጫረስ ከፍተኛ የሆነ አማራጭ ያለው ስልት መሆኑን አውቆታል።
በመቀጠል ለዚህም ላካሄዱበት እያካሄዱበት ላለውም ጥናት ከሚንስትር መስሪያቤቶችም ሆነ ጠቅላይ ሚንስትሩ መስሪያቤት እስከ ታች ድረስ በሙስና ተጨማልቀው ሀገሪቱን ለውጭ ድርጅት ወስጣዊ ደህንነቷን አሳልፈው ሰጥተዋል ሲሉ ሀሳባቸውን ቋጭተዋል።
ፖሊስ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር ዛይድ ወልደገብርኤልንና ያለመከሰስ መብታቸው በዛሬው እለት በፓርላማ የተነሳው የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር ዴኤታው አቶ አለማየሁ ጎጆን በዛሬው እለት በቁጥጥር ስር አዋለ።
ዛይድ ወልደገብርኤል ከሁለት አመት በፊት ከኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርነት ተነስተው ዋና ጽህፈት ቤቱን ሞንትሪያል ካናዳ ባደረገው አለም አቀፍ የስቪል አቬሽን ድርጅት; የኢትዮጵያ ቋሚ ተወካይ ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸው ይታወሳል።
ማለዳ ታይምስ

Thursday, August 3, 2017

የህወሓት “መከላከያ ሰራዊት” በበቃኝ ጥያቄ ተወጥሯል፤ ጄኔራሎች አሉበት!

July 3, 2017

ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው ህወሓት የሚመካበትን የታጠቀ ሰራዊት የሚመሩ ከፍተኛ መኮንኖችና ጄኔራሎች በጡረታ ለመሰናበት ጥያቄ ማቅረባቸው ተሰማ። የአስቸኳይ አዋጁ ሲነሳ መልስ እንደሚያገኙ ቃል የተገባላቸው እንዳሉም ታውቋል።
የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ለደህንነት ሲባል መረጃውን ያገኘበትን ሳይገለጽ እንደጠቆመው “መከላከያ ሰራዊት” የሚባለውን የህወሓት ሥልጣን አስጠባቂ የታጠቀ ኃይል ከሚመሩት ጄኔራሎች መካከል “በቃኝ” ያሉት ጄኔራሎች ከሰባት በላይ ሲሆኑ፣ በከፍተኛ መኮንን ደረጃ ያሉት ግን ቁጥራቸው በርከት ያለ ነው።
ጄኔራሎቹ ሰራዊቱን ለመሰናበት ያቀረቡትን ዋና ምክንያት የመረጃ ሰዎቹ ቃል በቃል ይፋ ባያደርጉም፣ ከሰራዊቱ ጋር ላለመቀጠል ዕድሜ፣ ጤና፣ ጋብቻና ተያያዥነት ያላቸው ጥያቄዎችን እንደ ምክንያት አቅርበዋል። መልቀቂያ ያስገቡት ብቻ ሳይሆኑ በርካቶች ተመሳሳይ ፍላጎት እንዳላቸውም ጠቁመዋል። የዚህም ምክንያቱ ሥርዓቱ አያያዙና አሁን የደረሰበት ደረጃ ለራሳቸውና ለቤተሰቦቻቸው ሰላም አስጊ በመሆኑ ነው።
በህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ውስጥ ባለው የኃይል አሰላለፍ ስጋት ውስጥ የገቡና ችግሩ ሊወሳሰብ እንደሚችል በማሰብ አድፍጠው በመጠባበቅ ላይ ያሉ ከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮች ሲሰናበቱ አገር ውስጥ የመኖር ዕቅድ እንደሌላቸውና ለዚሁም አስቀድመው የጉዞ ዝግጅት ያደረጉ እንዳሉም ተጠቁሟል።
ጥያቄውን የተቀበለው ውሳኔ ሰጪ አካል ለጊዜው የሰጠው ቁርጥ ያለ መልስ የለም። በአስቸኳይ አዋጁ ምክንያት ሰራዊቱን የመልቀቅ ጥያቄ በመመሪያ በመታገዱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መነሳት ተከትሎ ውሳኔ ሰጪዎች ምን እንደሚመለሱ ሊታወቅ እንደሚችል የመረጃው ሰዎች ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ነገረዋል።
በሰራዊቱ ውስጥ በሚታየው መረን የወጣ አድልዎ የተማረሩና የተሰላቹ ከፍተኛና መካከለኛ የመስመር መኮንኖችን ጨምሮ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሰራዊቱ አባላት ስንብት እንደሚፈልጉ በመረጋገጡ በወታደራዊ ውሳኔ ሰጪዎችና ፖሊሲ አውጪዎች ዘንድ ስጋት ፈጥሯል
በዚህም የተነሳ የአገልግሎት ጊዜያቸውን ጠቅሰው ስንብት የጠየቁ በከፍተኛ ደረጃ ክትትል እየተደረገባቸው መሆኑ ታውቋል። “አገሪቱ አሁን ባለችበት ችግር ውስጥ፣ አስቸኳይ ጊዜ ላይ እያለን እንዴት ስንብት ለመጠየቅ አሰብህ” በሚል እንደሚገመገሙም ከመረጃው ሰዎች ለመረዳት ተችሏል።
በሰራዊቱ ውስጥ ያለውን የ“በቃኝ” ህገ መንግስታዊ ጥያቄ በአስቸኳይ አዋጁ ስም አንቀው የያዙት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ሰራዊቱን ፍልሰት እንዳያርደው ፍርሃቻ ስለገባቸው ከወዲሁ የአዳዲስ ሃይል ምልመላ ሲያካሂዱ እንደነበር ለመረዳት ተችሏል። ከዚህም በላይ በየክልሉ ያለውን የልዩ ሃይል ከአስችኳይ ጊዜ መነሳት በኋላም በአንድ ዕዝ ውስጥ የማስገባት ስራ እንደሚሰራ ታውቋል።
እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሰራዊቱ አባላት የመሰናበት ፍላጎታቸውን አፍኖ መዝለቅ ስለማይቻል “ከጥልቅ ተሃድሶ በኋላ” በየክልሉ አዳዲስ ታጣቂ የማስፈለፈሉ ስራ እየተሰራ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል። አሁን ባለው አሰራር ከመከላከያ መሰናበት የሚችለው በጋብቻ ወደ ውጪ አገር የሚሄድ ወይም ቀደም ሲል በማመልከት የትምህርት ዕድል ያገኘ ብቻ እንደሆነና ይህ መመሪያ መቼ እንደሚነሳ በግልጽ የተቀመጠ ነገር እንደሌለ የመረጃው ምንጮች ተናገረዋል።
የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምን አገዛዝ ወደ ፍጻሜው ለማምጣት እንዲረዳ “በመፈንቅለ መንግሥት” ሙከራ ሳቢያ በርካታ ጄኔራሎች ከሠራዊቱ ተወግደው ነበር። ይህ የተቀነባበረ ድርጊት ለህወሓት ወደ አዲስ አበባ መግባት ዕንቅፋት ይሆናሉ ተብለው የታሰቡን በቀላሉ “ከመንገድ የጠረገ” እንደነበር የሚታወስ ነው። አገር ውስጥ ባሉ የውስጥ አርበኞችና በውጭ አገራት የለውጥ ፈላጊ ሆነው በቀረቡ “ከሃዲዎች” ቅንብር ሳይካሄድ የከሸፈው መፈንቅለ መንግሥት የሚጠርገውን ጠራርጎ ካለፈ በኋላ ኮ/ሎ መንግሥቱ ከሥልጣን የመወገዳቸው ጉዳይ “የቀናት” ብቻ እንደሆነ “ያበሰረ” እንደነበር ብዙዎች የሚያስታውሱት ነው።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ሰበብ አድርጎ የታፈነው የህወሓት ጄኔራሎች “የበቃኝ” ጥያቄ አስቀድሞ ከሥልጣናቸው የተለዩትን፣ በተለያዩ የሃብት መሰብሰብ ተግባራት የተሰማሩትንና ወደፊታቸውን የሰበሰቡትን ሃብት እየበሉ ለመኖር ባሰቡት ዘንድ እንዲሁም በሥልጣን ለመቆየት በሚያስቡት ጭምር የተደበላለቀ ስሜትን ፈጥሯል። ሆኖም የጄኔራሎቹ “የበቃኝ” ጥያቄ መነሻ ምክንያት ከላይ የተጠቀሱት ብቻ ይሁኑ ወይም ሌሎች ያልተጠቀሱ መነሾዎች ይኑራቸው ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም። (ፎቶው “የበቃኝ” ጥያቄ ካቀረቡት ጋር ግንኙንት የለውም)
ከጎልጉል ድህረ ገጽ የተወሰደ