Wednesday, December 9, 2015

በረሃብ የተጎዳው ወገን ቁጥር በእርዳታ ድርጅቶች ዳታ 13 ሚሊዮን ደረሰ:: ቀየውን ጥሎ የሚሰደደው በርክቷል::

December 12,2015
ተለያዩ የሰሜን እና ምስራቅ ኢትዮጵያ ክፍላተሃገራት የተሰማሩ ከተለያዩ የአለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች የተገኙ ዳታዎች እንደሚያመለክቱት በድርቅ የተጎዳው እና በረሃብ አለንጋ እየተገረፈ ያለው ሕዝብ ቁጥር 13 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሪፖርት መሰረት በጥር 2016 አስረ አምስት (15 )ሚሊዮን እንደሚገባ ተረጋግጧል::የእርዳታ ድርጅቶቹ ሰራተኞች እንደጠቆሙት በምስራቅ ኢትዮጵያ ሃረርጌ ውስጥ ብቻ ካለፈው ወር ከነበረው የረሃብ ተጎጂ ወገን ቀር በዚህ ዲሴምበር 2015 65% ከፍ ብሌል::የተረጂዎች ቁጥር እና የምግብ አቅርቦቱ እንዳይጨምር የመንግስት ባለስልጣናት ጫና ይፈጥራሉ ያሉት ሰራተኞቹ ሕዝቡ ቀየውን ትቶ ወደ ከተሞች እየዘለቀ መሆኑን ይናገራሉ::
በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ እና በአገው ልዩ ዞን እንዲሁም በአዲስ ዘመን አከባቢ ያለው ሁኔታ ከሌሎች የባሰ ሲሆን ከምስራቅ በለሳ እና ከአገው ምድር ሰቆጣ ቀያቸውን ጥልው በረሃብ ምክንያት የተሰደዱ በጎንደር አዲስ ዘመን ተሰፈሩ መሆኑ ሲታወቅ በትግራይ እንዲሁ እስካሁን እርዳታ ያላገኙ አከባቢዎች እንዳሉ ተጠቁሟል:: በአዲስ ዘመን ያሉ የብኣዴን ባለስልጣናት ከሰቆጣ እና በለሳ ተሰደው የሄዱትን ወገኖች መንግስት በያላችሁበት በጀት እየመደበ ስለሆነ በሚል ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ በማስገደድ ላይ መሆናቸው ታውቋል::ባለፈው ሳምንት በትግራይ በእንደርታ ወረዳ ለሚገኙ በድርቅ ለተጎዱ ተብሎ የመጣው ኣንድ እስካንያ መከኒ ከነተጎታቹ የእርዳታ እህል በወረዳው ባለስልጣናትና ነገዴዎች በመመሳጠር የተራገፈ ኣስመስለው በሌላ መኪና ገልብጠው ጭነው ሲወስዱ የኲሓ ህዝብ እጀ ከፈንጅ ይዞ ለፖሊስ ማስረከባቸው ይታወሳል::

No comments: