Tuesday, April 15, 2014

በባሌ 2 ሙስሊሞች በመንግስት ቅጥር ነብሰ ገዳዮች ሕይወታቸው መጥፋቱ ተዘገበ

April 15/2014

በባሌ ዞን ጊኒር ከተማ 2 ሙስሊሞች በመንግስት ቅጥር ነፍሰ ገዳዮች መገደላቸውንና ህዝቡ በከፍተኛ ሁኔታ ቁጣውን እየገለጸ እንደሆነ ቢቢኤን ራድዮ ዘገበ።

እንደራዲዮው ዘገባ ችግሩ የተከሰተው ሁለት የመንግስት ፖሊሶች በትላንትናው እለት ሰይፉ የተባለ ሙስሊም ኢትዮጵያዊ በጊኒር ከተማ በሚገኝ ሆቴል መኝታ ክፍል ይዘውት ከገቡ በኋላ በገመድ አንቀው የገደሉት ሲሆን የሆቴሉ ሰራተኛ መኝታ ቤቱን ሲከፍት ሟችን በማየት ለዘመዶቹ ጥቆማ ሰጥተዋል፡፡

ራድዮው ጨምሮም ሁኔታውን የሰማው ያካባቢው ነዋሪ በነቂስ በመውጣት ግርግር የተፈጠረ ሲሆን አስተዳደሩንም በመውረር ልጁን ይዘው ሲሄዱ የነበሩ ፖሊሶችን እንዲያቀርቡዋቸው፤ አልያም ሌላ ነገር እንደ ሚከሰት በመግለጽ ቢጠይቁም የመንግስት ቅጥረኞች ህዝቡን ከማረጋጋት ይልቅ ህዝቡ ላይ የተኩስ እሩምታ በመክፈት አብዲ በያን የተባለን በመግደል ቀውሱን አባብሰውታል ሲል ዘግቧል።

ቢቢኤን እንዳለው የሟቾቹም ሬሳ ለምርመራ በሚል አዲስ አበባ በሚገኘው ሚኒልክ ሆስፒታል ተልኳል፡፡

ዘ-ሐበሻ

No comments: