Monday, September 30, 2013

Ethiopia opposition stage anti-government demo


September 30/2013


.
A leading Ethiopian opposition group gathered Sunday to protest against the country's anti-terrorism legislation, the head of the group said.
???We want the government to abrogate the law and to release all political and prisoners of conscience immediately,??? Negasso Gidada, the leader of the opposition Unity for Democratic Justice (UDJ), told AFP.
Several opposition members and journalists, including dissident blogger Eskinder Nega, have been jailed under the 2009 legislation.
The government accused the group of ???glorifying??? convicted criminals and said the threat of terrorism in Ethiopia needed to be taken seriously.
???These people are downplaying the danger that this country has been facing... its not a potential threat, it's already there,??? said government spokesman Redwan Hussein.
Negasso said he was briefly arrested ahead of the protests along with the single member of parliament from an opposition party, Girma Seifu, and 60 other people.
Redwan said he did ???not know of anybody??? who had been detained.
The demonstration is part of a three-month campaign launched by UDJ, which has held protests in several cities across the country.
Negasso estimated the crowd at 80,000 people, while Redwan said only a few hundred had gathered.
The group, led by five people dressed in prison uniforms, chanted slogans demanding freedom and the release of prisoners, including UDJ member Andualem Arage who is serving a life sentence after he was convicted under the law.
Rights groups have accused Ethiopia's anti-terrorism legislation of being vague and used to stifle peaceful dissent.
Last year, two Swedish journalists jailed on terror-related offences were released after serving 13 months of their 11-year sentence.

Friday, September 27, 2013

የመንግስት የደህንነት መስሪያ ቤት ከወልድያ ሙስሊም ተማሪዎች አመጽ ጀርባ ሼክ ሙሀመድ አላሙዲን አሉበት አለ

መስከረም ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት ፣ “ኢህአዴግን የፈተነ ወሳኝ ክስተት” በማለት የገለጸውን የሙስሊሞች እንቅስቃሴ አልሻባብ፣ አልቃይዳ ፣ ግንቦት ሰባት ፣ እና የኤርትራ መንግስት እንደሚደግፉት በተደጋጋሚ በመገናኛ ብዙሀን ቢገልጽም፣ ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ ደግሞ የደህንነት ሀይሎች ቱጃሩን ሼክ ሙሀመድ ሁሴን አላሙዲንን ከእንቅስቃሴው ጀር...ባ እንዳሉበት የሚጠቁም መረጃ ለመንግስት ባለስልጣናት ማቅረቡ ታውቋል።

 በቅርቡ በወልድያ ከተማ የወልድያ ሙስሊም ተማሪዎች ባነሱት አመጽ መንገድ ዘግተው ወደ ላሊበላ ፤ ሰቆጣ ፣ ደሴ እና አዲስ አበባ የሚደረጉ የትራንስፖርት ጉዞዎች እንዲስተጓጎሉ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡


 ከዚሁ ጋር በተያያዘ አመጹን አነሳስታችሁዋል የተባሉ 13 ታዳጊ ወጣቶች በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ የደህነነት ሐይሎች አጣራነው ባሉት መረጃ አመጹን ሼክ አላሙዲን ከጀርባ ሆነው ደግፈውታል።


 የኢህአዴግ አመራር እና የፌደራል ፖሊስ የጋራ የጸረ ሽብር ግብረ ሐይል በጉዳዩ ዙሪያ በሰፊው ውይይት ካደረጉበት በኃላ ፣ በባለሀብቱ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ባይቻልም በወዳጆቻቸው በኩል ምክር አንዲሰጣቸው በአቶ በረከት ስምኦን የሚመራ አንድ ቡድን መዋቀሩን ለማወቅ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።


 ሼክ አላሙዲን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከታክስ እና ከግንባታ ጋር በተያያዘ ከመንግስት ጋር ውዝግብ ውስጥ መግባታቸው ይታወቃል። የደህንነት መስሪያ ቤት በባለሀብቱ እንቅስቃሴ ዙሪያ መረጃ እንዳገኘ ቢገልጽም፣ መረጃውን እንዴት እንዳገኘው አልታወቀም። አንዳንድ ወገኖች ግን የሼክ አላሙዲን ከህግ በላይ መሆን ያሳሳበው መንግስት፣ አጋጣሚውን በመጠቀም ባለሀብቱን ለመምታት የፈጠረው ዘዴ ሊሆን ይችላል ይላሉ።


 በጉዳዩ ዙሪያ ሼክ አላሙዲንን ወይም ወኪሎቻቸውን ለማግኘት ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።

 ሼህ አሊ አላሙዲን ለኢህአዴግ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይታወቃል።

Thursday, September 26, 2013

እንደ ቆራጥ ንስር ፓይለቶቹ…

September 26 / 2013

ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያውያን ዘንድ ዋና የመነጋገሪያ አርዕስት የነበረው አራት የአየር ሃይል አብራሪዎችና አስልጣኝ መኮንኖች ከዘረኞቹና ከዘራፊዎቹ ጎራ ወጥተው ወደ ነፃነት ታጋዮች ጎራ የመቀላቀላቸው ጉዳይ ነበር። እነዚህ ቆራጥና አገር ወዳድ አብራረዎች የወሰዱት እርምጃ ወገንን የሚያኮራና ከፍተኛ ጀግንነትን የሚጠይቅ ትልቅ ውሳኔ ነው።ይህ ውሳኔ ሰው ባጣች አገር፤ጀግና ባጣች አገር፤ለአገር ለወገን ተቆርቋሪ ባጣች አገር ውስጥ ትልቅ ተስፋ ሰጪ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ በያለበት በተለያየ መንገድ ይህን የጀግና ውሳኔ የወሰኑ ልጆቹን እያደነቀም እያመሰገነም ይገኛል::
የግንቦት ሰባት ንቅናቄም ይህን የጀግና ውስኔ የወሰኑ ወንድሞቹን እንኳን ተወለዳችሁ፤ እንኳንም ተማራችሁ፤ እንኳንም ወደ ነፃነቱ ትግል ተቀላቀላችሁ እያለ ደስታውንና ለጀግኖቹ ያለዉን ከፍተኛ አክብሮት ይገልፃል። ውሳኔያችሁ ከፈርዖን ቤተ-መንግስት ምቾት ይልቅ ከህዝቤ ጋር መሰደደ ይሻለኛል ያለውን የታላቁን ሰው የሙሴን ውሳኔ ይመስላልና የወሰዳችሁትን ትክክለኛ እርምጃ ትውልድ ምን ግዜም አይረሳዉም።
የእነዚህ ቆራጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ልጆች፣ ሙያና ችሎታ ስጋዊ የሆነ ፍላጎታቸውን ለማርካት ከበቂ በላይ ነው።ከዘረኞቹና ከቃየላውያኑ ቡድኖች ጋር እየተሞዳሞዱ ለመኖርም የሚሳናቸው አልነበሩም።ሆኖም ግን ዘረኞቹ(ህወሃቶች) የሚፈፅሙትን ግፍ ተሸክመው ፤ብኩርናቸውን ሽጠው እና ከሰው ተራ ወርደው ለመኖር ሂሊናችው አልፈቀደላቸውም።ለሚበላና ለሚጠጣ ከንቱ ነገር ብለው ጥቂት ዘረኞችን ተሸክሞ ከመኖር ይልቅ የነፃነቱን መንገድ መርጠዋልና ጀግኖች ብለን ብናወድሳቸው ተገቢ ይሆናል። እንዲህ ዓይነቱን ውሳኔ የሚወስን ሃሞተ ኮስታራ ጀግና እንጂ ሌላ አይደለም።
አሁንም ለራሳችሁ ክብር ያላችሁና ተመሳሳይ እርምጃ ለመዉሰድ በዝግጅት ላይ የምትገኙ የአገር መከላከያ አባላት እንዳላችሁ እናውቃለን። ቅምጥሎቹ ጄኔራል ተብየዎች ከድሃ ወገኖቻችሁ ላይ የዘረፉትን ዘርፈው አገሪቷን ጥለው መሄድ ጀምረዋል። ቀሪዎችም የዘረፉትን የድሃ ንብረት ወደ ውጪ አገር እያሸሹ እንደሆነም ይታወቃል።በአጠቃላይ በእናንተ ምርኩዝነት አገራችንን እያፈራረሷት፤ህዝቧንም እያወረዷት ነው።የህዝቡም መከራና እሮሮ ተወርቶ የሚያልቅ አይደለም።እንዲህ አይነቱን ግፍና በደል እያዩ ከንፈር መምጠጥ እያበቃ ነው።እንግዲህ አሁን እኔ ብቻየን ምን አደርጋለሁ የሚባልበት ግዜ እያለፈ ነው።ጋሻ መከታ እና የኋላ ደጀን የሚሆኗችሁ ብዙ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዉያን በየቦታው አሉ።ብትወድቁ የሚያነሷችሁ፤ብትደሙ ደማችሁን የሚያብሱላችሁ፤ብትሰው መስዋእትነታችሁን ለትውልድ የሚዘክሩላችሁ ወገን አለላችሁ።አትፍሩ። ከዘረኞቹ መንደር ወጥታችሁ የነፃነቱን ትግል እንድትቀላቀሉ ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርብላችኋለን።
ህውሃት ማለት የዘራፊዎች እና የጨካኝ ነፍሰ ገዳዮች ስብስብ መሆኑን ያለምንም ጥርጥር ማመን አለባችሁ።ህወሃት ስንቱን አርዶ፤ስንቱን ገድሎ፤ስንቱን አጥፍቶ፤የስንቱን ኑሮ በትኖ፤ስንቱን ዘርፎ ባዶ እጁን አስቀርቶ በትረ ስልጣኑን እንደያዘ ምስክር የሚያስፈልገን አይደለም።
የህውሃት ዘረኝነትና ዝሪፊያ የቆጨህ እና ለራስህ ክብር ያለህ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ተነስተህ ትግሉን ተቀላቀል።እነዚህን ግፈኞች የሚፈፅሙትን በደል እያዩ ዝም ማለት ግፉን ከመደገፍ ተለይቶ የሚታይ አይደለም።እናንተ ለራሳችሁ፤ ለወገናችሁና ለአገራቸችሁ ክብር ያላችሁ ዜጎች ዝም በማለታችሁ ህወሃቶች ዝምታችሁን እንደ በጎ ፈቃድ ቆጥረውት የግፍ ሰይፋቸውን ወደ ሰገባው ሊመልሱ ፈቃደኞች አልሆኑም።በማን አለበኝነታችውም ፀንተው ቆመዋል።እነዚህን ግፈኞች በቃ ለማለት ግዜው ደርሷልና የነፃነቱን ትግል ሳትዘገዩ አሁኑኑ ተቀላቀሉ።
እኛም ወደ ነፃነት ትግሉ እንድትቀላቀሉ ጥሪ ስናደርግላችሁ ለአገራችን ክብርና ለወገኖቻችን በሰላም መኖር ስንል ቆርጠን የተነሳን መሆናችንን ልንገልጽላችሁ እንወዳለን።የግንቦት ሰባት ንቅናቄ በምንም ሁኔታ በዘረኞች እጅ ተንቆና ተዋርዶ መኖርን አይቀበልም።እንዲህ ዓይነቱን ውርደት ተቀብሎ ለመኖር ሰው መሆናችን ይከለክለናል።እነዚህን ዘራፊዎች ተሸክመን ከመኖር ከነፃነታችን ጋር አያቶቻችን በተሰውበት ተራራ ላይ ቆመን መሰዋትን እንመርጣለን።አሁን ተነስተናልና የሚያቆመን የለም። እግዚአብሄርም መንገዳችንን ያከናውንልናል። ኑ ሀገርን ለማዳን የነጻነት ትግሉን ጎራ ተቀላቀሉ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

A must-watch ESAT Special on Ginbot 7 Meeting in Washington DC (Part 1)

         September 26, 2013           




Editor’s NoteOn Sunday September 22, 2013, the Ginbot 7 leadership had a very revealing and open discussion in Washington DC meeting like it has never had before . As you know, the issue of working with Eritrea has been a bone in the throat for G7 as well as for its supporters around the world. Many have argued against using Eritrea as a spring board to wage an armed struggle against TPLF.

Opponents claim that Eritrea can not be trusted based on their experience with Isayas Afeworki so far and his public rhetoric as it relates to Ethiopia. They may have a point. But the problem is that they don’t practice the position they defend or argue for. They don’t provide an alternative and actually implement that alternative. For example, they don’t answer to the question of where to wage an armed struggle and show us the way by an example.  They don’t. For instance, what don’t they find a place within Ethiopia and wage an armed struggle? What do they go and practice what they preach instead of simply analyzing and arguing from the comfort of their homes in the West. What they do is simply disagree and sometimes with bitterness and even animosity against G7 position towards Eritrea.
Instead of making an honest and logical attempt to convince and win our support, those who oppose G7′s position in Eritrea use intimidation, name callings, insults, put downs and inuendos to impose their opinion on G7 and its supporters. But the irony is that these forces claim to believe and fight for democracy in Ethiopia and yet they impose their position on others. G7 has repeatedly expressed the right of any political entity to follow a path it believes in without imposing its policy or belief on any one else except asking their support.

G7 has often made clear that it does not oppose other political parties who pursue a political path different than its own. It is interesting whether we know how to win support with a clean logical argument backed by results in the ground instead of an endless ineundos and name callings. 

Those who opposes G7 are not all  in the same wave length. Pro-TPLF mercenaries like Awramba Times editor are going against G7 to accomplish their paid assignments. There is no surprise about them. They are part of the package. There is also a second group that questions and suspects a multi-national political force like G7 for fear of revenge by TPLF victims in the form of genocide or a lesser nationwide violence against the Tigrian population.

 These group has a legitmate fear. But opposing such a political force as G7 is not a solution to their fear. In fact, a force such as G7, if strengthened, may help stabilize the country by preventing a possible chaos and ethnic violence in Ethiopia when TPLF collapses.

And there is a third group. These are political organizations who are competing for power in Ethiopia after TPLF. They believe if they don’t cook the dish, it does not taste good. They want power at any cost and by any means necessary. They are ego-driven and uncompromising. Nothing satisfies them until they are in power to implement their belief. They oppose everything any opponent does. They deliberately or honestly believe that truth is on their side. Doing so is wounding their ego and it is relinquishing the possibility of power in Ethiopia.

There is one final group which I consider innocent but suspicious. Our story with Eritrea is full of suspicions and actual heart-breaking experience due to the war waged between Ethiopia and Eritrea for over 40 years now. They don’t trust anything related to Eritrea no matter who said what including God. These group has a legitmate concern but suspicion should not tie our hands and prevent us from doing what needs to be done. Our situation today is desperate. TPLF has done and still doing all it can to destroy our people and country. These suspicioius group should know that there are times in life when you have to do what you got to do to get out of a rock and hard place by swallowing our pride and controlling our suspicion.There is a saying in our country,” ቀን እስኪአልፍልህ የአባትህ ባርያ ይግዛህ” that we should follow. These group has no alternative except to give it a try while holding its suspicions. At this point, all of us have one universal enemy. And we have to focus on it. And that is TPLF. And it is wise to talk about our differences after we free Ethiopia from TPLF by any means necessary.

The G7 leadership has directly presented the question in a ‘take it or leave’ it manner to the audience and the Diaspora watching on ESAT.

Berhanu and Andi 5

Click the image above to watch the G7 meeting in DC on September 22, 2013

Ato Andargachew Tsige, secretary of G7, has explained in detail about the Eritrean question during the meeting. It may be hard to tell if every body is convinced. With all their suspicions remaining, there is no doubt many may be considering to give G7′s policy on Eritrea a chance, if it has any possibility of working, given the dire and critical circumstances Ethiopia has found itself at this time. 

There is no sure thing in life as well as in struggle. You take chances and you take risks. Not a blind risk but a pragmatic one based on the circumstances you found yourself boxed in. Not taking that risk, no matter how difficult, is committing a self-inflicted suicide. You put all your options on the table. And you pick the one with the least risk. And then you move on.

 And if not, the choice is to get stuck in some meaningless and fruitless activity and continue to waste time, money and even lives for nothing and finally give up and be forgotten. G7 seems to have made a decision to take the least risky option, according to Ato Andargachew Tsige, and is pursuing it with resolve. 

And for those of us with an apposing view, let us do what we believe in without imposing our position on G7 and its policy towards Eritrea. According to Ato Andargachew Tsige, G7 is not imposing its position on any person or political entity. He said they don’t oppose the positions other political organizations are taking when it comes to Eritrea or any other political position.

The take home message is that, we in the opposition camp, should all follow our individual political choices in our quest to remove TPLF from power without attacking each other. We all don’t have to come to the same conclusion. Let us just disagree without being disagreeable. There is no need to vehemently be involved in slash and burn campaign against a position we don’t agree on. First, it is not democratic. Second, it is nasty. We will sound like the dictators we claim to hate like Mensgistu and Meles. No one party or person has the monopoly on the truth of what works best to bring TPLF down. The only way to establish that truth is based on the results of a given policy on the ground. And let us all give a chance, with patience, to see what works with our suspicions still intact

ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብትን ሊገድብ ይችላል የተባለ መመሪያወጣ

protest 2
September 26 /2013

ከቅርብ ወራት ወዲህ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የአደባባይ የተቃውሞ ሰልፍ መጥራት መጀመራቸውን ተከትሎ በኢትዮጽያ ሕገመንግስት አንቀጽ 30 መሰረት የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና አቤቱታ የማቅረብ መብትን ሊገድብ ይችላል የተባለ አዲስ መመሪያ የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር ማውጣቱ ተሰማ። አዲሱ መመሪያ ሰላማዊ ሰልፍ የማይደረግባቸው አካባቢዎችንና ጊዜያትን ለይቶ ያስቀምጣል።

 በዚሁ መሠረት በሃይማኖት ተቋማት፣ ሰፊ ህዝብ በሚገበያይባቸው የገበያ ቦታዎችና ህብረተሰቡ በብዛትና በስፋት በሚንቀሳቅስባቸው የስራ ቀናት እንዲሁም በስራ መግቢያና መውጫ ስዓታት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ እንደማይፈቀድ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አካላት ገልፀዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም ህገ መንግስቱ ላይ የሰፈሩትንና ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግናበመሰብሰብ መብት ላይ ያተኮሩትን ሀሳቦች በዝርዘር ማየቱ አስፈላጊ በመሆኑ፤ ህገ መንግስቱን በአግባቡለመተግበር የሚያስችል መመሪያ ማዘጋጀቱን ገልጿል።
 በውስጡም ህጉን በዝርዝር ለማስፈፀም የሚያስችሉ መመሪያዎችን ያካተተ ነው ተብሏል።
ሰላማዊ ሰልፉን የጠራው አካል ያሉበትን ሃላፊነቶችና  የፀጥታ አካላትን ሚና ምን እንደሆነ በዝርዝር ያስቀመጠ መሆኑ ታውቋል።
የመመሪያው ተልዕኮ በህገ መንግስቱ አንቀፅ 30  ላይ የተቀመጠውን ድንጋጌ ማስፈፀምእንደመሆኑ ሁሉም ዜጋ በቅርቡ እንዲያውቅ ይደረጋል ብለዋል።
በዚሁ አንቀፅ ንዑስ ቁጥር 1 ላይ የሰፈረው ድንጋጌ ደግሞ ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋርበመሆን መሳሪያ ሳይዝ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ እንዳለበት ያስቀምጣል።

ከቤት ውጪ የሚደረጉ ስብሰባዎችና ሰለማዊ ስልፎች በህዝብ እንቅስቃሴ ላይ ችግርእንዳይፈጥሩ ለማድረግና ሰላምን፣ ዲሞክራሲያዊ መብቶችንና የህዝብን የሞራል ሁኔታ እንዳይጥሱአግባብነት ያላቸው ስርአቶች ሊደነገጉ እንደሚችሉ በህገ መንግስቱ ላይ ተቀምጧል። 

የሰላማዊ ሰልፍና የፖለቲካ ስብሰባ አዋጅ ቁጥር 31/83 ኢህአዴግ ወደሥልጣን እንደመጣከወጡ አዋጆች አንዱና ቀዳሚው ነው:: ይህንኑ መብት የሚያረጋግጥ ተጨማሪ ድንጋጌ በ 1987 አ.ምበአዋጅ ቁጥር 1/87 በጸደቀው ህገ መንግስት አንቀጽ 30 ስር ተቀምጧል:: በዚህ ሕግ መሰረት ሰላማዊሰልፍ ለማድረግ የሚፈልግ አካል ከ 48 ሰአት በፊት በአቅራቢያው ለሚገኘው የመስተዳድር አካልማሳወቅ እንዳለበት መስተዳድሩ ደግሞ የሰልፈኛውን ደህንነት የሚጠብቅ የጸጥታ ሀይል የመመደብ ግዴታየተጣለባቸው ሲሆን ሰልፉን በታቀደበት ቀን ለማካሄድ የማያስችል በቂ ምክንያት በተገኘ ጊዜመስተዳድሩ ይህንኑ በመግለጽ ስብሰባው ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ ኀሳብ ማቅረብ እንደሚችል በአዋጁተመልክቷል:: በሰላማዊ መንገድ ተሰብስቦ ተቃውሞን መግለጽ ህገ መንግስታዊና ሰብአዊ መብት በመሆኑይህንን መብት የሚንድ መመሪያ የአዲስአበባ አስተዳደርም ሆነ የፌዴራሉ ም/ቤት የማውጣት በህገመንግስቱ የተሰጣቸው መብት እንደሌለ አንዳንድ የሕግ ባለሙያዎች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ይህ መመሪያ መውጣቱን ከአዲስአበባ ፖሊስ መረጃ ካገኘ በኋላ የፖሊስ ከፍተኛ አመራሮችንና የአዲስአበባ አስተዳደር ኃላፊዎችን በጉዳዩ ላይ ለማነጋገር ሞክሮ እንዳልተሳካለት በይፋ መግለጹን በተለይ በግሉ መገናኛ ብዙሃን መዘገቡ ይታወሳል። የፓርቲው አመራሮች መመሪያ የወጣው የተቃዋሚዎችን በተደጋጋሚ ሰልፍ ለመውጣት የመጀመሩትን ጥረት ለማፈን ነው ማለታቸው ይታወሳል።

በጉዳዩ ላይ አስተያየት የጠየቅናቸው አንዳንድ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች መመሪያ ወጥቷል መባሉን ከመስማት ውጪ ኮፒው ስላልደረሳቸው አስተያየት ለመስጠት እንደሚቸገሩ ተናግረዋል። ሆኖም በአንዳንድ መገናኛ ብዙሃን ያነበቡትና የሰሙት ዓይነት መመሪያ ወጥቶ ከሆነ ሕገመንግስታዊ መብትን የሚገድብ መሆኑ የሚያጠራጥር አይደለም ብለዋል።
  


አንድነት ሰላማዊ ሰልፉን ለማካሄድ አራት አደባባዮች በአማራጭነት አቅርቦ እየተነጋገረ ነው

Septemper 25/2013

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ ጠርቶት የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ የከተማው አስተዳደር በአደባባዩ ዙሪያ ኮንስትራክሽን እየተከናወነ ስለሆነ አደባባዩ ማንኛውንም ሰልፍ ስለማያካሂድ ጃንሜዳ በአማራጭነት በማቅረቡ የአንድነት ሰልፍ በመስቀል አደባባይ ማካሄድ አስቸጋሪ ሁኔታ መፈጠሩን ፓርቲው አስታወቀ። የከተማው አስተዳደር የአዋጁን አንቀጾች ጠቅሶ ፓርቲው በመስቀል አደባባይ ሰልፍ ማካሄድ እንደማይችል በመግለፅና አማራጭ አማራጭ እንዲያቀርብ መጠየቁ፤ ከጃንሜዳ እና ከመስቀል አደባባይ ውጪ ሌሎች አራት አደባባዮች በአማራጭነት አቅርቦ ከአስተዳደሩ እየተነጋገረ መሆኑን የፓርቲው የብሔራዊ ምክር ቤት ዋና ፀሐፊና የሕዝባዊ ንቅናቄ ግብረ-ኃይሉ ፀሐፊ አቶ ትዕግስቱ አወሉ ለሰንደቅ ጋዜጣ ተናግረዋል።

ፓርቲው መስቀል አደባባይ የተከለከለበት ሂደት አሳማኝና ሞራላዊ ባይሆንም ፓርቲው እራሱ መስቀል አደባባይን ጨምሮ ሌሎች አራት አደባባዮችን በአማራጭነት ለማየት ከአዲስ አበባ አስተዳደር ጋር ለመነጋገር መገደዱን ገልፀዋል። ፓርቲው በአማራጭነት ያቀረባቸው አደባባዮች የኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት አደባባይ፣ ቴዎድሮስ አደባባይ፣ አራት ኪሎ እና ስድስት ኪሎ አደባባዮች መሆናቸውን በመጥቀስ ከተቻለ የአዲስ አበባ ስታዲዬምም እየታየ መሆኑን አመልክተዋል።

ቀደም ሲል ሰልፉን ቀበና ከሚገኘው የፓርቲው ጽ/ቤት መነሻ የማድረጉን ነገር በመቀየር ከተመረጡ ክፍለ ከተሞች ከተለያዩ ቦታዎች ወደ አደባባዮች ሕዝቡ እንዲሰባሰብ መወሰኑን ገልፀዋል። ፓርቲው በሰልፉ ይሳተፋል ብሎ የገመተው ግማሽ ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ከአደባባዮቹ ስፋት ጋር ባይመጣጠንም ሰልፉ በጎዳናዎቹ ላይ ጭምር የሚከናወን መሆኑን አመልክተዋል።

አንድነት ፓርቲ ጃንሜዳ ላይ ሰልፉን የማያካሂደው በሁለት ምክንያት መሆኑን አቶ ትዕግስቱ ገልፀዋል። የመጀመሪያው በሰላማዊ ሰልፍ አዋጅ ቁጥር 3/1983 ዓ.ም አንቀፅ 7 ንዑስ ቁጥር 2 መሠረት ሰላማዊ ሰልፍ መካሄድ ያለበት ከጦር ካምፓች ቢያንስ 500 ሜትር ርቀት ላይ ነው። ነገር ግን ጃንሜዳ በመቶ ሜትር ርቀት ላይ ትልቅ የጦር ካምፕ በመኖሩ በቀጥታ አዋጁን መጣስ ነው የሚሆነው። ሁለተኛው ምክንያት ቦታው ሣር የበቀለበት ረግረጋማ ስፍራ በመሆኑ በአጠቃላይ ጃንሜዳ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ከሕግም ሆነ ከአመቺነት አንፃር ተመራጭ ባለመሆኑ ነው ብለዋል።

“ሰልፉ በምንም አይነት አይቀርም” ያሉት አቶ ትዕግስቱ አንድነት ፓርቲ የሕዝቡን መብት በድርድር እየጠየቀ አይደለም ብለዋል። ስርዓቱ ፍፁም አምባገነናዊ ስርዓት በመሆኑ አንድነት የተገኘውን ቀዳዳ ሁሉ ሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ በሆነ መንገድ እንደሚያስኬድ ገልፀዋል።
“አንድነት ሰላማዊ ትግሉን ከዲፕሎማሲያዊ ድርድር ጋር ይዞ ነው የሚሄደው” ያሉት አቶ ትዕግስቱ፤ በሰልፉ ቦታ ላይ ከመንግስት ጋር መደራደሩ ለመንግስት የመንበርከክ ጉዳይ አይደለም ብለዋል።

ለጊዜው የሰልፉ ቦታ ባይለይም ኅብረተሰቡ በሰልፉ ላይ እንዲሳተፍ በሦስት ተሽከርካሪዎች የጎዳና ላይ ቅስቀሳ መደረጉን፣ በቤት ለቤት፣ በማኅበራዊ ድረ ገጽ በሌሎች የመቀስቀሻ መንገዶች ቅሰቀሳ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል። እንዲሁም ለንግዱ ማኅበረሰብ በልዩ ሁኔታ ጥሪ መደረጉን ገልፀዋል። በተጨማሪም በከተማዋ ውስጥ የሚገኙ መዋቅሮች ስልጠና ተሰጥቷቸው በእንቅስቃሴ ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ሰላማዊ ሰልፉ የ1997ቱ ሰልፍ የሚያስታውስ ሰልፍ እንደሚሆን ተስፋ መኖሩን አመልክተዋል።

በሰልፉ ላይ ለመነሻ ያህል አምስት መቶ ሺህና ከዚያ በላይ ሕዝብ የሚሳተፍ ቢሆንም፤ በመንግስት በኩል ፓርቲው የተቃውሞ ሰልፍ በጠራበት ዕለት በተመሳሳይ በየትምህርት ቤቱ የወላጆች ስብሰባ መጥራቱ አግባብ አለመሆኑንም አቶ ትዕግስቱ ተናግረዋል። የወላጆች ውይይት መስከረም 5 ቀን 2006 ዓ.ም ቀደም ሲል አንድነት ሰልፍ በጠራበት ዕለት ተጠርቶ የነበረ ቢሆንም፤ ባልታወቀ ምክንያት ወደ መስከረም 19 ቀን 2006 መቀየሩ ሆን ተብሎ የፓርቲው ሰልፍ ላይ እንቅፋት ለመፍጠር ነው ብለዋል።

ሰልፉ የፍትህና የነፃነት ጥሪ መሆኑን ያስገነዘቡት አቶ ትዕግስቱ የፀረ ሽብር ሕጉ እንዲሰረዝ፣ የኑሮ ውድነቱና ስራ አጥነት እንዲቀረፍ፣ የታሰሩ ጋዜጠኞችና የፖለቲካ መሪዎች እንዲፈቱ፣ በልማት ስም የዜጎችን መፈናቀልን የሚቃወምና መብቱን የሚጠይቅ ማንኛውም ኅብረተሰብ እንዲካፈል ጥሪ መቅረቡን አመልክተዋል። የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ጥያቄ ከፀረ-ሽብር ሕጉ በተለየ ሁኔታ የሚያያዝ በመሆኑ ሕጉ እንዲሰረዝ ፍላጎት ካላቸው ጎን ይቆማሉ የሚል እምነት እንዳለ ጠቅሰዋል። በሰልፉ ላይ መኢአድ ከአንድነት ፓርቲ ባልተናነሰ ሁኔታ በሰልፉ መሳተፉንና 33ቱ ፓርቲዎች ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑንም ጠቁመዋል።

አንድነት ፓርቲ ከተመሠረተ አራት ዓመት ቢሆነውም የቀድሞው ሊቀመንበር ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ እንዲፈቱ 250 ሰዎች የተካፈሉበት ሰልፍ ማድረጉ አይዘነጋም። ባለፉት ሦስት ወራትም በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መሪ ቃል ሰልፎችና ሕዝባዊ ውይይት ማድረጉም አይዘነጋም::

Wednesday, September 25, 2013

እስራቱ ቀጥሏል ፖሊሰ የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዘንዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳን አሰረ

September 25/2013

ከገዛኸኝ አበበ
 
እስራቱና ቅስቀሳው መሳ  ለመሳ እየሄዱ ነው ::  አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ መስከረም 19, 2006 በመስቀል አደባባይ ለሚያደርገው ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በዛሬው ዕለት በሞራል እና በንቃት በቅስቀሳ ስራ  ላይ ተሰማርተው  እያሉ ሁል ጌዜ ህዝብን ማሸበር ማሰር እና ማሰቃየት ስራው የሆነው የወያኔ መንግስት በበኩሉ ፖሊሶቹን በማሰማራት  በዛሬው ዕለት ለቅስቀሳ ከወጡ መኪኖች ሁለተኛው በቄራ መታገቱንና በቅስቀሳ ስራ ተሰማርተው የነበሩ አባላት በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርገዋል፡፡

ይህ እንዲህ ባለበት ሁኔታ የቀድሞ የአገሪቱ ፕሬዘንዳንት የነበሩት የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ፕሬዘንዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳን ፓሊስ ያሰራቸው ሲሆን ዶክተር ነጋሶ የታሰሩበት ምክንያት የፓርቲውን የቅስቀሳ ቡድን አባላት ለማስፉታት ወደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ የሽሮ ሜዳ ፖሊስ ማዘዣ ጣብያ በማምራት ለፖሊሶቹ ልጆቹ ምንም የፈጸሙት ህገ ወጥ ድርጊት ስለሌል እና ልጆቹም ሲቀሰቅሱ የነበረው በመንግስት እውቅና የተሰጠውን ሰላማዊ ሰልፍ ነው ቅስቀሳው ህገ ወጥ ነው የምትሉም ከሆነ እነዚን ወጣቶች የላኳቸው እኔ ስለሆንኩኝ እኔን ልታስሮኝ ትችላላችው በማለቸው ፖሊሰ የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዘንዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳን በማሰር ወጣቶቹን የለቀቀቸው መሆኑን ለማወቅ ችለናል :: 


ነገር ግን የአንድነት ፓርቲ አባላት እና ቅስቀሳው ላይ የተሰማሮት ግለሰቦች በምንም የሚበገሩ አይመስሉም በትናትናው እለት  መንግስት ቅስቀሳውን ለማስተጓጎል ከ28 በላይ አባላትን አስሯ ፓርቲው የተከራያቸው የቅስቀሳ መኪኖች ታርጋቸውን በመፍታት ዳግመኛ ስራ እንዳይሰሩ በትራፊክ እንዲቀጡ ቢያደረግም የመኪና ባለቤቶቹ ፣ ሾፌሮቹና ረዳቶቻቸው “ስራችን ስለሆነ ብቻ ሳይሆን ጭምር ዓላማችሁንም ስለምንደግፍ ከጎናቹ ነን ምንም አይነት ነገር ቢመጣ ወደ ኋላ አንልም” ማለታቸው ይታወሳል፡፡

  The Voice of Freedom



Woyane got it all wrong; it has no way out but the unconditional surrender for democratic rule

September 25, 2013

The Ethiopian regime seems to misunderstand what the people of Ethiopia are demanding. The sooner the regime gets it and surrender peacefully for democratic rule the better it would be. Playing hide-and-seek game isn’t going to do it.  Spewing empty ethnic and religious propaganda isn’t going to save it. Hiding behind corrupt investments and empty growth propaganda isn’t a substitute for freedom. Tormenting the population and jailing the innocent with empty bravado isn’t going to help it form its inevitable demise. Woyane and its stooges must appreciate the tolerance of our people and accept the illegitimacy of the ruling regime and live with it. Noting will change that reality. 

Hailemariam Desalegne, the Prime Minster appointed to replace Melseby Teshome Debalke
 
Stupidity is a virtue brought about by ignorance, empty self-worth and bravado; often exhibited in a circle of people in-and around tyrannies, gangs and rouge groups that rely on intimidation and brut force to sustain their existence.  Therefore, the Ethiopian ruling regime known for its stupidity and brutality on the top of its organized corruption has no qualm to remain on the bottom of the pits since it came to power. Its apologists aren’t far behind; not willing to rise up to the occasion when the rotten regime reduces them to impersonator beyond recognition.
 
When the self-declared minority regime implemented Apartheid to insure its survival it was bound to commit atrocities and corruption beyond an average tyranny. When the apologist lie through their teeth to cover up for its crimes it was clear illustration of how a confined ethnic audience can be manipulated to play on the bottom. Therefore, the Woyane regime has one thing going for it; a collection of ethnic yes-men clapping with one hand and stealing with the other to make enough noise for the world to believe there is something out of noting.  
 
There is no discord among Ethiopians the rogue regime rotted beyond repair long ago and banking on its killing and extortion machine to get by. Naturally, the more people say so the more deadly the regime became with no one around its apologists capable of pushing it out of the bottom it chose to play.
 
Obviously Woyane made its bed and slept in it for too long. The question that remained is how is it there are still people out there that entertain to hold on to a rotten ethnic regime-fully aware of its criminality? In other words, what could possibly motivate people to remotely associate with a self-declared Mafia on the top of an Apartheid regime to stick around in unwinnable battle against the people of Ethiopia?
 
The behavior of the regime’s apologists-glued with the self distractive regime is uncharacteristically abnormal. It is another indication they are in a do-or-die situations to prevent the inevitable demise of the Apartheid regime. Woyane’s attempts to kill and bribes its way out of the demand for democratic rule and sustain its corrupt practices aren’t a small matter for anyone to ignore just because of an elaborate village propaganda that doesn’t worth the paper it is written on. 
 
The debate among Ethiopians continued as the struggle reached a point of no return. Some, my self included believe Woyane is acting on behalf of foreign interest-out to stick around as long as its sponsors allowed it. Others believe it is another opportunist regime that uses ethnicity and cronyism to  hold on  its political and economic power. And, many others believe it is a racist group that wishes ‘Tigrians’ to dominate the lives of the rest of Ethiopians through division and organize corruption.
Though all arguments are true when one observes the behaviors and actions of the regime at one time or another there is one burning question that begs for an answer. Why would a regime that declared itself a representative of a minority ethnic group wants to isolate its constituency from the larger community by pretending to benefit them through atrocities and corruption is where the question must be asked and answered by none other than Tigrians the regime claims to represent.   After all, unless Tigrians collectively buy into sustaining the Apartheid system implemented by none other than TPLF in their name would benefit them, TPLF is as good as dead.  In reality, there is no worst insult to the people of Tigray than being represented by a rouge group with the army of cadres and assassins corrupted to the hilt.
The idiocy of Woyane and its apologists
\
If one thing is clear it is the audacity of Woyane and its apologists’ insult to the intelligence of our people. The people of Ethiopia have endured the insults and atrocities of a self declared Tigrian group and its apologists over and over again for over two decades.  Fortunately, it is strictly confined around relatively small circle of ethnic elites that are prone for violence and corruption-uncharacteristic of the average Ethiopian experience. What is even more amusing is the apologist unprecedented level of arrogance and dedication to legitimize a rotten regime’s criminality as progress.
 
In the history of the struggle for democracy no one group spoke for anyone but itself. If it claims to do so it is unquestionably tyranny in the making.  As evident, Woyane proved us beyond a reasonable doubt a rogue group is unworthy of democratic representation.
\
Therefore, any group that claims anything less than the universal suffrage of our people and democratic rule is as dangerous as Woyane for our society and the world at large as Woyane proved us allover again.  Reducing the essence of democracy to bottom of the pits for political expediency isn’t only an insult to the people but it is crime against humanity.  
 
Woyane is obviously unprincipled ethnic drifter- a moving target that operates from its comfort zone under the slogan of Ethnic Federalism. It is constantly in search of its next meal and a place to hide. Its only pride is the possession it scavenged and robed from the public as it roams the streets bullying and extorting the population. Its nomadic existence is justified by the ethnic drifters it surrounds itself; scavenging and robbing in their own rights in the name of Ethnic Federalism.  
 
Ever since the legendry ethnic drifter of TPLF departed that guided the pack of ethnic warlords, Woyane is in disarray of its own making while its ethnic apologists are disoriented. Ethnic Federalism that was designed to sustain the rogue TPLF led regime is becoming a nightmare to sustain Apartheid.   Therefore, no one can deprive TPLF and its apologist a hiding place better than Tigrians the rogue group used and abused and hide behind for the last 22 years.  
 
Not in my name
 
The unconventional rule of the rogue group should surprise anyone or the excuses its apologists come up with to sustain the rogue regime. But, the apathy of the rest of us not to call a spade a spade to agree on what needs to be done to end the hapless regime’s rule became its meal ticket to remain for so long.
 
But, noting would come close to Tigrians’ collective declaration of ‘not in my name’ to bring Apartheid down once for all. After all, if the rogue group is deprived a hiding place what good could it be but, a desperate mercenary? 
 
Lately, the ethnic warlords are disoriented enough to throw rocks in every direction to see if they can save the Apartheid regime they helped established from its inevitable demise. Some are wondering in-and out of their designated ethnic comfort zone. Others are pushing the ‘envelop’ to the limit to see if it works to extend the life of the regime. Some are running for their life before they become the causality of the monster they help created and benefited. A few are attempting to fake reconciliation while blaming and jailing the innocent. And, the rest are wondering what their fate would be-with all the crimes under their belt.   At this point in time whatever they do and say is irrelevant to be taken seriously. As far as Ethiopians are concerned Woyane is as good as dead; searching for ways to revive it or take the rest of us with it.
\
Make no mistake; the hapless regime’s stooges are scared to their pants for the crime they committed on the people of Ethiopia. They are hoping by complicating matters further it would help them deceive their way out their crime. No one is doing them a favor more than those rushing to get advantage of the bribe the regime offers and other that take the regimes propaganda face value.  Ethnic peddlers-segregating our peoples as if the rules of law and democracy have ethnic identity aren’t helping.  With all honesty, the ethnic elites got it all wrong. The last thing they would peddle in Ethiopia should be ethnicity but the rule of law and democracy. After all what good would it do to our people creating collections of ethnic tyrannies than democratic Ethiopia?
 
The lust for power peculiarly makes people bypass individuals’ right and the rule of law in search of self gratification; peddling for anything that makes them relevant.   The Woyane elites are a classic prove of’ shooting own foot and crying wolf. Thank God our people are way ahead of our elites to see the bigger picture of demanding the rule of law than being a stepping stone for the adventure of rogue groups. After all, who lost the most in the adventure of our contemporary elites’ quest climb to power in the last five decades? The wisdom of our people is beyond bound. It is time us to learn a lesson or two we never find recycling books and reinventing the wheel.
 
Looking at the frightened Woyane ethnic elites’ boundless excuses to fit their lust for power and corruption-bypassing the freedom of our people is disgusting. They are desperate and clumsy enough offering condominium for the gullible is a substitute for freedom and democracy. It illustrates the crises our society endures with our contemporary elites’ adventure to eat their cake and having it too. They look and talk progressive but act as if they walked out of Stone Age in the era of the Information Revolution and democracy.
 
Their latest hoax of terrorism is a continuation of dodging the demand to surrender power for democratic rule without committing more crime than they already did on our people.  Let face it, no two faced ethnic tyranny would protect us from our own people in the name of terrorism. The fact Ethiopians are protecting each other from the rogue regime that terrorize us is an indication Ethiopians don’t need protection from each other but the regime.
 
The time has come Woyane step down. The apologist would also be better off to speed up its demise for their own sake.
 
Ethiopians will get a legitimate government. There is no if-and-but about it.

Birhanu and Andargachew: Victims of their own deceptions (Public meeting highlights)

Birhanu Nega and Andargachew Tsige: Victims of their own deceptions. Highlights of Ginbot 7′s public meeting in Washington DC, Sunday September 22, 2013.

Andargachew and Birhanu
Ginbot 7 chairman Dr. Birhanu Nega and secretary general Andargachew Tsige (Photo Abaymedia)


ከለውጡ በኋላስ? (ጋዜጠኛ ተመሰገን ደሳለኝ )

September 24, 2013

Journalist Temasegan Dasalegኢህአዴግ ወደ መጨረሻው ምዕራፍ (በውስጥም በውጪም ተግዳሮቶች) መገፋቱን በሚያመላክቱ የፖለቲካ አጀንዳዎች ላይ የሚያጠነጥን አንድ ፅሁፍ (‹የአብዮቱ የምፅዓት ቀን ምልክቶች›› በሚል ርዕስ) አቅርቤ እንደነበር ይታወሳል፤ ይዘቱም በመጪዎቹ ወራት ወይም ዓመት ስርዓቱ ‹ምርጫ› አሊያም ‹ህዝባዊ› እምቢተኝነት ከሚያመጣው ‹ማዕበል› (እንደበረከት ስምዖን አገላለፅ ‹ናዳን በሚገታ ሩጫ›) የማምለጥ ዕድሉ የጠበበ መሆኑን የሚያመላክት ነው፤ ይሁንና አንድ አብዮት ታላቅ (ውጤታማ) ሊባል የሚችለው አምባገነን ስርዓትን በመቀየሩ ብቻ ስላልሆነ (ሥር-ነቀል ለውጥ የሚፈጥር አብዮት ዋጋ የሚኖረው የዲሞክራሲ ተቋማትን መሰረት መጣል ሲችል ነውና) በቀጣይ መፃኢ ዕድሉ ላይ መነጋገሩ አስፈላጊ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡
በዚህ ፅሁፍህ ተጠየቅም ‹ከስርዓቱ ለውጥ በኋላ፣ ማን ነው አማራጩ?› የሚለው ጥያቄ ትኩረት ይደረግበት ዘንድ አመላክታለሁ፡፡

 ምክንያቱም በጠለፉ መንገድ ከቀሩ አብዮቶች ታሪክ ተምረን፣ ‹መጥነን ካልደቆስን› የሚከፈለውን ዋጋ በብላሽ የሚያስቀር አሳዛኝ ሁናቴ ሊፈጠር ይችላልና (ቭላድሚር ኤሊች ሌኒን ‹‹አብዮት፣ ለአብዮት ብቻ ሲባል መካሄድ የለበትም›› እንዲል፣ ከኢህአዴግ መገላገሉ መልካም ቢሆንም፣ የአገላጋዩን ማቀፊያ ከወዲሁ መምረጡ ወይም የምንጠይቀውን ማወቁ ብልህነት ነው)

አማራጩ ተወልዷልን?

ከኢህአዴግ በኋላ የሚተካው አማራጭ ተዘጋጅቷል? …ይህንን ቀዳዳ አስቀድሞ መድፈኑን አስቸኳይ ያደረገው፣ ለውጡ የሚመጣበት መንገድ ‹ከህዝባዊ እምቢተኝነት› ይሆናል የሚለው ቅደመ-ግምት ነው፡፡ ከታዓማኒና በዕኩል አሳታፊ ምርጫ የሚነሳ ሽግግር (‹ሕዝብ የሚፈልገውን ያውቃልና ውሳኔው መከበር አለበት› ከሚለው የዲሞክራሲ ፅንሰ-ሃሳብ በመነሳት) አሳሳቢነቱ ከአደባባይ ተቃውሞ የሚመነጨውን ያህል አይደለም፤ ስለዚህም ከስጋት ነፃ መሆን የሚቻለው በሰላማዊ መንገድ ለመታገል መሰረታቸውን ሀገር ቤት አድርገው በህግ የተመዘገቡ የፖለቲካ ድርጅቶች የቤት ስራቸውን ሰርተው ዝግጁ ሆነው ሲጠብቁ ብቻ ነው፡፡ ይህ ግን የድርጅቶቹን ቁጥር ከሰማኒያ በላይ ከማሻቀብ ያለፈ አስተዋፅኦ የሌላቸውን አሰስ-ገሰስ ‹ፓርቲ›ዎች በሙሉ እንደሚመለከት ተደርጎ መወሰድ የለበትም፡፡

 ነፍስ ይማርና በ‹‹ልዕልና ጋዜጣ›› እልፍ አእላፍ ችግሮቹን ማረም ከቻለ መድረክ ተስፋ ሊጣልበት ይችላል ብዬ እንደማስብ መፃፌን አስታውሳለሁ፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የመድረክ አሰላለፍ ሊቀየር በማጋደሉ (ከአንድነት ጋ አብሮ መቀጠሉ ማጠራጠሩ) እና ሰማያዊ ፓርቲ አዎንታዊ እንቅስቃሴ ከማድረጉ አኳያ ተፎካካሪ ሊሆን የሚችልበት ዕድል በመፍጠሩ፣ በአጀንዳው ላይ ማካትቱን ተገቢ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ ይሁንና ሌሎች ፓርቲዎችን እዚህ ጋ ያላነሳሁበት፣ ከላይ ከጠቀስኩት በተጨማሪ ሶስት ምክንያቶች አሉኝ፤ ቅቡልነትን ማጣት፣ እንቅስቃሴ አልባ መሆን እና በገዥው ፓርቲ ስፖንሰርነት መተንፈስ የሚሉ፡፡

መድረክ

የስድስት ፓርቲዎች ስብስብ ነው፤ በምርጫ ሁለት ሺህ ሁለት (ምንም እንኳ ከአንድ የምክር ቤት ወንበር በላይ ባይሳካለትም) ከሁሉም

 ተቀናቃኞች በላይ ጐልቶ መውጣት ችሎ እንደነበር ይታወሳል፡፡ የአምስተኛውን ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫም ተስፋ አድርጎ ለመጠበቁ
ማሳያዎቹ፡- አንድም ስብስቡ ዛሬም ህላዊ መሆኑ፣ ሁለትም ለበርካታ አባላቱና ደጋፊዎቹ ወደ ‹ግንባር ተሻጋገሩ› ግፊት ምላሽ መስጠት
መቻሉ ነው፡፡

 በምስረታው ዋዜማና
ማግስት ብዙ የተነገረለት መድረክ እርስ በእርሱ (በአንድ ጠርዝ-የአንድነት አመራሮች፤ በሌላኛው-ኦፌኮ እና
ኢሶዴፓ) የፈጠረው ውዝግብ በዙሪያው ለተሰለፉ አባላትና ደጋፊዎች ተስፋ አስቆራጭ ነው፡፡ ለግንባሩ ቅርብ የሆነ ወዳጄ የችግሩን
መጦዝ የገለፀው ‹‹ሁለቱ ጎራዎች በስብሰባ ወቅት ‹በውሃ ቀጠነ› ለፀብ ሲገባበዙ የሚያይ እና ለስድብ የሚጠቀሙባቸውን ቃላት የሚሰማ በአንድ ግንባር የተሰለፉ ናቸው ብሎ ከሚያምን ‹ግመል በመርፌ ቀዳዳ መሽሎኩን› ቢቀበል ይቀለዋል›› በሚል ምፀት ነው፡፡ አደጋውን የከፋ የሚያደርገው ደግሞ ኩነቶቹ ከመለዘብ ይልቅ መባባሳቸው ይመስለኛል፡፡

በመሬት ያለው እውነታ ይህ ቢሆንም፣ ፓርቲው በ2005 ዓ.ም ወርሃ መጋቢት ወደ ‹ግንባር› መሻገሩን ከማብሰሩም በላይ፣
‹‹የኢትዮጵያን ወቅታዊና መሰረታዊ ችግሮች የመፍቻ አጋጣሚዎች›› በሚል ርዕስ ይፋ ባደረገው ባለአራት ገፅ ‹ማኔፌስቶ›፣ የሀገሪቱን

 ችግር በሙሉ በአራት ክፍል ቀንብቦ ካስቀመጠ በኋላ፣ ጉዳዩን ፈረንጅኛው ‹የሲኒ ማዕበል› እንደሚለው አድርጎ በማለፍ የ‹ደግፉኝ›

ጥሪውን እንዲህ ሲል አስተላልፏል፡-‹‹ይህንን ፀረ-ህዝብና ፀረ-ሀገር የሆነውን ኢህአዴጋዊ ስርዓት በሰላማዊ አግባብ በምታደርገው ብርቱ ትግልህ መለወጥ እንደምትችል ካለፈው የትግል ተሞክሮህ ሆነ የአለም ህዝቦች ለነፃነት፣ ለዕኩልነትና ለፍትህ ብሎም ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት እውን መሆን ከሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎችና ከሚያስመዘግቧቸውም ድሎች ትገነዘባለህ፡፡ ስለሆነም መድረክ ይህንን ክቡር ትግልህን በመምራት ባለቤትነት እንድትበቃ በፅናትህ ከጎንህ ሆኖ ለመታገለ መወሰኑን ተገንዝበህ ከምንጊዜም በላይ ሁለንተናዊ ድጋፍህን እንድትሰጥ ጥሪያችንን በከፍተኛ አክብሮትና በአንተም ላይ ባለን ሙሉ እምነት እናስተላልፋለን፡፡››በግሌ መድረክ ራሱ በሁለት ምክንያቶች እምነት ሊጣልበት የሚችል አልመስለኝም፡፡

የመጀመሪያው ከአንድነት ጋር የገባበት ድምፅ የለሽ ውዝግብ ከዕለት ወደ እለት እያደገ መሄዱ ነው፤ አዲሱ የዶክተር መረራ ጉዲና መጽሐፍም ቅራኔውን ቢያሳፋው አይገርምም፤ ዶ/ሩ ስለ2002ቱ ምርጫ ባወሳበት ምዕራፍ ‹‹የ1997ቱ የቅንጅት ወራሽ ነው ብለን የተማመንበት አንድነት እውነተኛ ወራሽ ለመሆን በጣም ብዙ እንደሚቀረው ተረዳው›› ያለበት ግምገማ እና ‹‹ያልገባኝና የሚከነክነኝ አንድነት ኦሮሚያ ላይ በብዛት ያወዳደራቸው ኦህዴድ ያሰማራቸው ወሮበሎች ነበሩ›› ፍረጃው ‹ትችት›ን በቅንነት ለመቀበል ልምድ ከሌለው የሀገሪቱ ፖለቲካ አንጻር አቧራ ማስነሳቱ አይቀሬ ለመሆኑ መገመቱ አይከብድም፡፡ ይህ እንግዲህ አንድነትን የአማራ (የከተማ ልሂቃን) ተወካይ የሚያደረገውን ወቀሳ ሳይጨመር ነው (እዚህ ጋ የሚነሳው አስቂኙ ጉዳይ ወቀሳውን የሚሰነዝሩት አባል ፓርቲዎች አንድነት የብሔር ድርጅት ቢሆን ይበልጥ ተጠቃሚ ከመሆናቸው በተጨማሪ ለአብዛኛው ችግሮቻቸው በቀላሉ መፍትሄ የመስጠቱ ጉዳይ ሲታሰብ ነው) ሁለተኛው መድረኩ ከለውጡ በኋላ ሀገር ለመምራት የሚያስችል የጠራ የፖለቲካ አመለካከት አለመከተሉ ነው፤ በውስጡ ያሉ ፓርቲዎች ቢያንስ ሁለት የተለያዩ ፕሮግራም የሚያራምዱ መሆናቸው ይታወቃል፡፡

የአንድነትን እና የኦፌኮን ፕሮግራም ብንወስድ

የችግሩን ግዝፈት ያሳየናል፤ አንድነት መልካ ምድር ላይ ስለተመሰረተ ፌደራሊዝም አስተዳደር ጠቀሜታ ሲያብራራ፤ የኦፌኮ ባለስድስት ገፅ

 ፕሮግራም ደግሞ በማንነት ላይ ስለተመሰረተ ፌደራሊዝም ይሰብካል፡፡ በግልባጩ ውድሀት ይፈፅሙ እንዳይባል ደግሞ የእነ ዶ/ር መረራ

‹ከተዋህድን ኦሮሞ ተውጦ ይጠፋል› ስጋት ጋሬጣ ነው፡፡ አንዳንድ የአመራር አባላቱ ‹‹ዓላማችን ቅድሚያ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን
መገንባት ነው›› የሚል መከራከሪያ ሲያቀርቡ ቢደመጡም፣ ከዚህ በኩል ከሚነሳው ተግዳሮት በቀላሉ የሚመለጥ አይመስለኝም
(በነገራችን ላይ መድረኩ በወቅታዊው ቁመና ‹ግንባር› ለመመስረት የሚያስችለውን መስፈርት ሟሟላቱ ራሱ አጠራጣሪ ነው)

አንድነት

የአንድነት ተግዳሮት ወደ መድረክ ከመግባት ጋ ተያይዞ የመጣ ነው (ከጠዋቱ ሰማያዊ ፓርቲን የመሰረቱት ወጣቶች ከድርጅቱ
ለመውጣት አንዱ ምክንያታቸው ይህ እንደሆነ ይታወሳል)፤ ትብብሩን ‹ያልተባረከ ጋብቻ› የሚያስብለው ደግሞ የዛሬ አራት ዓመት ‹ወደ

 መድረክ ካልገባን ትግሉን እናደናቅፋለን› ሲሉ የነበሩ አንዳንድ የአንድነት አመራሮች የውዝግቡ ተሳፊ መሆናቸውን ስንመለከት ነው፤

 መተነኳኮሱ በ2002ቱ ምርጫ ማግስት የተጀመረ ቢሆንም፣ ባለፈው ዓመት ወደ መጦዝ ተሸጋግሯል፡፡ በተለይም አንድነት ‹‹የሚሊዮኖች

 ድምፅ ንቅናቄ›› በሚል መርህ ያካሄደው የሶስት ወር ዘመቻ መድረክን አለማካተቱ የሚያስተላልፈው መልዕክት ግልፅ ነው፡፡ በ‹‹ፀረ-

ሽብር›› አዋጁ ላይ (ኢህአዴግንና ኢዴፓን ጨምሮ) በተደረገው ክርክርም አንድነት እና መድረክ በተለያዩ ሰዎች ተወክለው መቅረባቸው

 ግንኙነቱን እንደ ቀድሞ ለማየት አስቸጋሪ አድርጎታል፡፡

ይህም ሆኖ አንድነት በራሱ የተሻለ ፓርቲ ሆኖ ሊወጣ የሚችልበት ዕድል አለው፡፡ ምሁራዊ ስብስቡም ሆነ የኢኮኖሚ አቅሙ
(የዲያስፖራ ድጋፉ) አንፃራዊ ጥንካሬ እንዲያገኝ ረድቶታል፤ ርዕዮተ-ዓለሙንም ከተቀናቃኝ ፓርቲዎች በጠበቀ መልኩ ማዘጋጀቱ
ለቅቡልነቱ አስተዋፅኦ ሊያደርግለት ይችላል፤ ከመኢአድ ጋር የጀመረውን ውህደት (‹የአማራ ተወካይ› የሚለውን ፍረጃ ቢያጠናክረውም)

ከዳር ካደረሰ ደግሞ ከአቻዎቹ ጋ ያለው ልዩነት በእጅጉ መስፋቱ አይቀሬ ነው (መኢአድ የፈራረሰው ከአናት ነውና ግዙፍ መዋቅሩ ‹እረኛ አልባ› በመሆኑ፣ አንድነት በውህደት ስም ቢሰበስበው በከፍተኛ ደረጃ ይጠቅመዋል)

የወል-መንገድ

 በቀጣይ የተሻለ አማራጭ ሆኖ ለመገኘት መድረክና አንድነት መቻቻላቸው ወሳኝ ነው፡፡ ይሁንና ኩነቱን በታዛቢነት መመልከት
የመረጡት የአረና ሰዎቸ በግንባሩ ቢሮ ሰላም ለማውረድ የአስታራቂነት ሚና ቢጫወቱ ጠቃሚነቱ ለእነርሱም ነው፡፡ አንድነቶችም፣
በመድረክ ስም እዚህ ድረስ ለመጓዝ የከፈሉት ዋጋ ብላሽ ከሆነ ማንንም አያተርፍም፡፡ በአናቱም ወቅታዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አስገዳጅ

 መሆኑ መረሳት የለበትም፡፡ ምክንያቱም አንድነት የሰበሰባቸው ልሂቃኖችም ሆኑ በሀገሪቱ የተለያዩ ከተሞች ያነበረው መዋቅር (ጥንካሬው
ላይ ያለኝ ጥርጣሬ እንደተጠበቀ ሆኖ) ቅድሚያ ለብሔር ፖለቲካ ከሚሰጡ አካባቢዎች በ‹መድረክ ባርኔጣ› በሚገኝ ድጋፍ (ድምፅ)
ካልታገዘ በቀር አየር ላይ ተንጠልጥሎ ከመቅረት አይታደገውም፡፡
 

 የመድረክ ተግዳሮትም ተመሳሳይ ነው፤ በፖለቲካው ላይ ውጤት የሚያዛባ ተፅዕኖ ማሳረፍ የሚቻላቸውንና አንድነት የራሱ
ያደረጋቸውን ከተሜዎች ‹ቡራኬ› ሳይቀበል ወደ ውድድር መግባቱ ‹ውሃ በወንፊት…› አይነት ሊሆንበት ይችላል፡፡ የመድረክንና
የአንድነትን የወል ቀዳዳ መዘርዘሩን እዚሁ ገትቼ፣ የተሻለ ጥንካሬና የመግባባት መንፈስ ለማስረፅ በቅድሚያ የችግሮቻቸውን መንስኤ
ለይተው ማወቅ አለባቸው ብዬ ስለማስብ፣ በግሌ ‹ያለመግባባቱ መነሻ› ከምላቸው ዋና ጉዳዮች ሶስቱን በአዲስ መስመር እጠቅሳለሁ፡፡

፩- የፕሮግራም መጋጨት ያመጣው ጣጣ አንዱ ነው፤ ይኸውም የፀቡ የቡድን አባቶች የ‹ሕብረ ብሔር› እና የ‹ክልል› ፖለቲካ አቀንቃኝነት፣ ሁሉም አባል ፓርቲዎች መድረኩን ሲፈጥሩ የየራሳቸውን ፕሮግራም እንደያዙ መሆኑ፣ ጥቂት የማይባሉ ልዩነታቸውን ሳይፈቱ ‹በይደር› ማስቀመጣቸው… እንደ ማሳያ ይጠቀሳሉ፡፡ ይህ ሁኔታም የእርስ በእርስ መተማማን እንዳይኖራቸው ያደረገ ይመስለኛል(ከዚህ አኳያም ለመፍትሄው ቅድሚያ ከልሰጡ በመድረክ በኩል ‹መጪው ጊዜ ብሩህ ይሆናል› ብሎ መጠበቅ ‹የዋህ› ሊያስብል ይችላል) የጫናው ተፅእኖ ደግሞ በሁለቱም በኩል (በአንድነትና በብሄር ድርጅቶቹ) ከሚከተሉት የፖለቲካ አመለካከት አንፃር ወደ ስልጣን የመምጣቱ አጋጣሚ ቢፈጠር፣ የታገሉለትን ስርዓት ማንበሩ ፍፁም አዳጋች መሆኑን በማስታወስ ነው፤ አንድነቶች ፓርቲያቸው ከመድረክ እንዲወጣ ይጎተጉታሉ፤ ብሔር ተኮሮቹ ደግሞ ‹አንድነት የነፍጠኛውን ስርዓት የሚመለስ በመሆኑ፣ ወይ ወደ ብሄር ድርጅት ራሱን ይቀየር፣ አሊያም ፕሮግራሙን ይከልስ› የሚለው ሙግታቸው በአሳማኝ ሁኔታ መፍትሄ አለማግኘቱ ራሱን የቻለ ሌላ ትግል ከሚፈልግ አጀንዳ ጋ አላትሟቸዋል፡፡

፪-አንድነት በሚያራምደው የሊብራል ዲሞክራሲ እና አብዛኛው የመድረክ አባል ድርጅቶች በሚከተሉት የሶሻል ዲሞክራሲ መካከል ያለውን ልዩነት የማሰታረቅ ስራ አለመሰራቱ ነው፡፡ ‹‹የአንድነት ፓርቲ ስትራቴጂና የአምስት ዓመት ዕቅድ›› በሚል ርዕስ 246 ገፅ ይዞ በታተመው መፅሀፍ ላይ ‹‹አንድነት የሚመሰረትበት ርዕዮተ-ዓለም ሊበራሊዝም ሆኖ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፖሊሲዎች የሶሻል ዲሞክራሲን ጠቃሚ ገፅታዎች ይወስዳል›› የሚለው አንቀፅ ቢጤን ለመልካም ግንኙነት መደላድል መሆን ይችላል (በነገራችን ላይ‹እንዲህ የችግር ቋት ተሸክመው ስለምን በጋራ ለመስራት ተስማሙ?› የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርምና ግምቴን ላስቀምጥ፤ የብሔር ድርጅቶቹን እስትንፋስ የሚቆጣጠሩት ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ እና ዶ/ር መረራ ጉዲና ምርጫ 97ን ከሁለት አቅጣጫ ገምግመው ከደረሱበት ድምዳሜ ጋ የሚያያዝ ይመስለኛል፤ ይኸውም ‹አንድነት፣ የቅንጅት ወራሽ ነው› የሚለው የተሳሳተው ትንተና አንዱ ሲሆን፣ ሁለተኛው በዛው ምርጫ ተቀማጭነታቸው አውሮፓና አሜሪካ ከሆኑ አስራ ሁለት ፓርቲዎች ጋር መስርተውት የነበረው ‹‹ህብረት››፣ ፓርላማ በመግባታቸው፣ ከውግዘት ጋር እንዲባረሩ በማድረጉ ያሳደረባቸው መገለል ሊሆን ይችላል፤ በአንድነት በኩል ደግሞ ‹የመድረኩ መሀንዲስ› ተደርገው የተወሰዱት ዶ/ር ነጋሶና አቶ ስዬ አብርሃ አንድነትን ለመቀላቀል ወደ መድረክ መግባትን እንደ መደራደሪያ በማቅረባቸው ሲሆን፣ ሌላኛው ደግሞ ዛሬም ያልተሸነፈው የ‹ተባበሩ ወይም ተሰባበሩ› ግልብ ግፊት ነው ብዬ አስባለሁ፤ የዚህ ድምር ውጤትም ከነርዕዮተ-ዓለም እና የፕሮግራም ልዩነት ወደ መድረኩ አምጥቷቸው አይን የሚገባ ሥራ እንዳይሰሩ አግዷቸዋል)

፫-የመድረክ አባል ድርጅቶች መተዳደሪያ ደንብን አለማክበር ‹የፖለቲካ ብልጠት› በማድረጋቸው፣ ለራሳቸው ተጨማሪ የመናተረኪያአጀንዳ ፈጥረዋል፡፡ ይህ አይነቱ ስርዓት አልበኝነት በጋራም በተናጥልም ተፈፅሟል፡፡ አንድነትን ጨምሮ የመድረኩ ስራ አስፈፃሚ ደጋግሞከመርሁ ሲያፈነግጥ ታይቷል፤ ለምሳሌ በደንቡ ላይ መሻሻል ያለበትን አንቀፅ የሚወስነውም ሆነ ከፍተኛው ስልጣን የጠቅላላ ጉባዔውመሆኑ በግልፅ ተቀምጦ ሳለ፣ ጉባዔው ከተሰበሰበባቸው በአንዱ ዕለት ‹የመድረኩ ሊቀ-መንበረ በዙር ከሚሆን፣ በብቃት ይሁን›፤እንዲሁም ‹አዲስ ፓርቲ በአባልነት የምንቀበልበት መንገድ መሻሻል አለበት› የሚሉ አቋሞች ላይ ቢደርስም፣ ስራ አስፈፃሚው ቃል በቃል‹ይህንን አሰራር ጉባኤው ሊቀይረው አይችልም› ሲል ውድቅ ያደረገበትን አጋጣሚ መጥቀስ ይቻላል፡፡

 በተናጥል አንድነት፣ ኦፌኮ እና ኢሶዴፓ በአንቀፅ 21 ‹የአባል ድርጅቶች ግዴታ› በሚል ርዕስ ስር የተቀመጡትን፡- ‹ከአፍራሽና
ተቃራኒ ከሆኑ እንቅስቃሴዎች መቆጠብ›፣ ‹በአባላት መካከል አለመተማመን ከሚፈጥሩ ማናቸውም ተግባር መቆጠብ›፣ ‹የግንባሩን አቋም

 የሚፃረር አቋም ያለማራመድ› እና መሰል ደንቦችን ደጋግመው በአደባባይ ሲጥሱ ታይተዋል፤ ይህ አይነቱ ስርዓተ-አልበኝነት መፍትሄ

 ሳያገኝ የተሻለና ጠንካራ ሆኖ መውጣቱ አዳጋች ይመስለኛል፡፡

ሰማያዊ

 ሰማያዊ ፓርቲ አዲስ በመሆኑ ለወቀሳ መቸኮሉ አግባብ እንዳልሆነ ቢሰማኝም፣ ፓርቲው እያሳየ ካለው ፈጣን እንቅስቃሴ አኳያ፣
በፍጥነቶቹ መካከል የሚፈጥራቸውን ድክመቶቹን ቢያሻሽል ጠቀሜታው ለሀገር ስለሆነ የግል አስታየየት መስጠቱን አስፈላጊ ሆኖ
አግኝቸዋለሁ፡፡የሰማያዊ ዋናው ድክመት ከ‹ግንፍሌ ፓርቲ›ነት አልፎ የመሄድ ፍላጎት ያለው አለመምሰሉ ነው (ጽ/ቤቱ አራት ኪሎ /ግንፍሌ/ አካባቢ ይገኛል)፡፡

 ከአዲስ አበባ ውጪ ለመንቀሳቀስ ሲሞክር አይታይም፤ በሌሎቸ የሀገሪቱ ከተሞች የተከፈተ ተጨማሪ ቢሮ ካለ፣ ከምስረታው
በኋላ የአባላቱ ቁጥር ምን ያህል እንደደረሰ፣ እና መሰል መረጃዎችን ለማግኘት ወደ ፓርቲው ጽ/ቤት ሄዶ የነበረው የመፅሄቱ ሪፖርተር

‹እንዴት እንደምትጠቀሙበት ስለማናውቅ አንናገርም› በሚል ክልከላ በመመለሱ ስለወቅታዊው ቁመና እዚህ ጋ መጥቀስ አልተቻለም

(ከዚህ ውጪ ሊቀ-መንበሩ ይልቃል ጌትነት ከ‹ሰንደቅ› ጋዜጣ ጋር ባደረገው ቃለ-መጠይቅ ‹‹ባለፉት 40 ዓመታት ከመጣው የፓርቲዎች ጥንካሬ ይልቅ፣ በአንድ ዓመት ውስጥ ሰማያዊ ፓርቲ ብቻውን አምጥጦታል›› ያለው ሀረግ ስህተት ቢሆንም፣ አንድም በሂደት የሚታረም፣ሁለትም የአፍ ወለምታ፣ ሶስትም ከልምድ ማነስ የሚያጋጥም በመሆኑ ‹ፀጉር መንጨቱ› ፓርቲው ፍርሃትን ለመስበር ከሚያደርገው እንቅስቃሴ አኳያ ገንቢ አይደለምና አልፈዋለሁ፡፡)

‹እምነት ጨምሩልን›

 ‹ለውጥ! ለውጥ!› የሚል ድምፅ በመላ ሀገሪቱ የበረከተው የ‹ቡርዣ› ወይም ‹አድሀሪ› አብዮትን በመናፈቅ አይደለም፤ እንዲህ አይነት

 አብዮት፣ ከሰው ለውጥ በቀር ሕዝባዊ ጠቀሜታ የለውማና፡፡ የደርግም ሆነ የኢህአዴግ ‹አብዮት› የዚህ አምሳያ በመሆኑ ነው፣ ዛሬም

 ዘመን ተጋሪዎቼ ‹ፋኖ ተሰማራ!› ከማለት ነፃ ያልወጡት፡፡ ‹ሶስተኛው አብዮት› የማይሸነፍ እና የማይንበረከክ እንዲሆንልን ከምንመኘው
በላይ ወደ ‹መፈንቅለ-መንግስት›ነት እንዳይቀየር መጠንቀቁንም ግዴታ ያደረገው ጠንካራ ፓርቲና የነቃ ማህበረሰብ ያለመኖሩ ስጋት ነው፡

 ፡ ይህ ደግሞ ከወዲሁ ከአማራጩ ኃይል ጎን መቆም ይቻል ዘንድ ‹እምነት ጨምሩልን!› (ሀገር የመረከብ አቅማቸውን አሳዩን?) እንድንል አስገድዷል (‹ጀግናው› ኢህአዴግ ወደ ማይቀረው ሽንፈት መንገዱን ከጀመረ ጥቂት ክረምቶች በማለፋቸው፣ ከለውጡ በኋላ የሚመጣው ኃይል ሁለንታው የተቃና መሆኑን ማስመስከር አለበት)መድረክ፣ አንድነት እና ሰማያዊ ወደራሳቸው ይመለከቱ ዘንድ ከሞላ ጎደል የወል ‹ክፍተቶች› ወይም ‹ድክመቶች› የምላቸውን ሶስት ጉዳዮች ከዚህ ቀጥሎ እጠቅሳለሁ፡፡

ሃሳብ-አልባ

 ፓርቲዎቹ በምስረታቸው ዘመን ቅድሚያ የሚሰጡት ለምርጫ ቦርድ የእውቅና ሰርተፍኬት እና ‹ተቃዋሚ ድርጅት› ተብለው
ለመጠራት በመሆኑ አንድም የሀገሪቱን አንኳር ችግሮች አጥንተው መፍትሄ በመያዝ አልተዘጋጁም፤ ሁለትም ከነባር ድርጅቶች ድክመትና

 ጥንካሬ ተምረው አልመጡም፤ በዚህም የሚፈልጉትን ሳያወቁ እና የተለየ አማራጭ ሳይይዙ ወደ ፖለቲካው ገብተዋል ወደሚል ጠርዝ

 እየገፋን ነው፤ ጠንካራና የተፍታታ የፖለቲካ ፕሮግራም የላቸውም፤ በንፅፅር ‹‹አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ›› የተሻለ ፕሮግራም
ለመቅረፅ ከመሞከሩ ውጪ፣ የመንግስቱ ስልጣን ‹ገጭ-ቋ› ቢል ‹አማራጭ ሊሆኑ ይችላሉ› የሚባሉት ፓርቲዎች ‹እያሾፉ ነው› በሚል

 ችላ ካልተባሉ በቀር ‹ፕሮግራሜ› ብለው ያቀረቡትን ለተመለከተ ምን ያህል ሃሳብ አልባ እንደሆኑ ለመረዳት አይቸገርም፡፡
የሆነው ሆኖ ይህንን ፅሁፍ ሳዘጋጅ የነበረኝ አመለካከት ስለመድረክና አንድነት የፖለቲካ ፕሮግራም ደካማነት ከዚህ ቀደም ስለጠቀስኩ፣

 ዛሬ ሰማያዊ ፓርቲን ብቻ አንስተን ብንነጋገር ይሻላል የሚል ነበር፤ ይሁንና የድርጅቱን ፕሮግራም ካነበብኩ በኋላ ግን ምንም ማውራት

 እንደማይቻል ተረዳው (ያውም ያየሁት ወረቀት ‹ፕሮግራም› ተብሎ ሊጠራ ከቻለ ማለት ነው)፡፡ ፓርቲው ለስልጣን የመብቃት ዕድል

 ካገኘ፣ ለዘመናት ሲንከባለልና ሲደራረብ የመጣውን ዘርፈ ብዙ የሀገሪቷን ችግር የሚፈታው ‹‹የሰማያዊ ፓርቲ ፕሮግራም›› በማለት ርዕስ
ባዘጋጀው ባለአስራ አምስት ገፅ ወረቀት ነው፡፡ መቼም በዚህ ፕሮግራም ‹ከሌሎች የተሻልኩ ነኝ-ምረጡኝ› የማለቱ ድፍረት ግራ አጋቢ

 ይመስለኛል፤ ምናልባት ‹የፖለቲካ ሳይንስ ምሁሩ ዶ/ር መረራ ጉዲና ካዘጋጀው አራት ገፅ ፕሮግራም፣ የእኛ የበለጠ ነው› የሚል
መከራከሪያ ካልቀረበ፡፡

 ስለርዕዮተ-ዓለሙም ቢሆን ‹ለዘብተኛ ሌብራሊዝም› ከማለት ያለፈ ያብራራልን ጉዳይ የለም (በዚህ በኩል ኢዴፓ ከሁሉም በተሻለ የተብራራና የጠበቀ ፕሮግራም አለው፤ ግና! ለአንድ ፓርቲ ከምንም በላይ አስፈላጊ የሆነውን ‹ታአማኒነት› አፍርሷልና ፕሮግራሙ ጠቀመ አልጠቀመ ፋይዳ አለው ማለት አይቻልም) በተቀረ ያለ ርዕዮተ-ዓለም ፓርቲ መስርቶ፣ ‹ሀገሬን፣ ሀገሬን…› ማለቱን

 ከቀረርቶ ለይቶ መረዳት ይቸግራል፡፡ መድረክ፣ አንድነት እና ሰማያዊ አሁንም ጊዜውም ዕድሉም አላቸውና ስልጣን ቢይዙ በዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች፣ በፖሊሲዎች፣ በማህበራዊ ፍትህ እና መሰል ጉዳዮች ላይ ያላችውን የመፍትሄ ሃሳብ እና የተሻለ አማራጭ በትክክል ተንትነው ማዘጋጀቱን ቢያስቀድሙ መልካም ይመስለኛል፡፡

ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ በ1997 ዓ.ም ‹‹የምርጫ ማኒፌስቶ›› ብሎ ያዘጋጀው ሰነድ እንኳ ከ130 ገፅ በላይ የፈጀ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው፡፡ እናም ፓርቲዎቹ ‹ፕሮግራሜ› የሚሉትንም ሆነ፣ ከተራራ የገዘፈ ችግሮቻችንን በደቃቃ ግምገማ ለማብራራት መዳከሩን አርቀው በመስቀል ወደ ቁም-ነገሩ ቢያዘንብሉ ጠቀሜታው ለራሳቸው ነው፤ ‹የትም ፍጪው…› መረሳት አለበት፤ ለፖለቲካ ፓርቲ ሃሳብ ከምንም በላይ ወሳኝ ነው፡፡ ዳሩስ! በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የተዘጋጀ ፓርቲ፣ የሚሸጥ ርዕዮተ-ዓለም ካላዘጋጀ በቀር ወታደራዊ ድርጅት አይደለምና ‹በኃይል ተጠቅሜ ፍላጎቴን አሳካለሁ› ሊል አይችልም፡፡ እውነት እውነት እላችኋለውም በዚህ በኩል ቀድሞ የነቃ፣ እርሱ አትራፊ ነው፤ ረቢው እንዳለውም ‹ላለው ይጨመርለታል›ና፡፡

ምሁር አልባ

የተፎካካሪ ድርጅቶች ሌላኛው ክፍተት ምሁራንን /ሙያተኞችን/ አለማቀፍ እንደሆነ ተደጋግሞ ቢነገርም፣ ዛሬም በዚህ በኩል የተሰራ

 ሥራ የለም፡፡ ይህንን ቀዳዳ ለመድፈን አመራሩና አባለቱ ከጽ/ቤት በመውጣት መቀስቀስ፣ ማሳመን፣ ማግባባት… አለባቸው ብዬ
አስባለሁ፤ መቼም በሁሉም ዘርፍ ‹እኔ ብቻ ነኝ የማውቀው› ግብዝነትን የወረሱት ነፍሱን ይማረውና ከአቶ መለስ ይመስለኛል፤ ይህ
አይነቱ አመለካከት ግን ወንዝ አያሻግርም፡፡ በርግጥ ‹ፖለቲካና ኮረንቲ…› በሚባልበት አገር፣ በደፍረት፣ ድርጅት እስከመመስረት መድረስ

 ትልቅ ታሪክ ቢሆንም፣ ጠንካራ መሆን ካልተቻለ ዞሮ ዞሮ ያው ክሽፈት ነው፡፡ አደባባዩም እንደቀድሞ ‹ድንጋይ ዳቦ ነው› ብለው
ለሚከራከሩ አፈ-ጮማ ፖለቲከኞች ቦታ የሌለው መሆኑ ግልፅ ይመስለኛል፡፡ በተለያየ ሙያ የሰለጠኑ ምሁራኖችን ወደ ፓርቲያችሁ
ለመሳብ መደላደሉን አመቻቹ፤ ፍርሃት መሰበር እንዳለበት አሳምኗቸው፤ አንኳኩ፤ ከልከፈቱም ደጋግሙት፡፡

የሴራ ፖለቲካ

ሌላው ድርጅቶቹ የሚጠነክሩት፡- ከሴራ፣ ከስርቻ ስር ፖለቲካ፣ ከጠልፎ መጣል ጨዋታ፣ ከአፍቅሮተ-ስልጣን አና ከመሳሰሉት ነፃ
ሲሆኑ ነው፡፡ በአናቱም የጥናትና ምርምር ዘርፍ መሰል እያቋቋሙ እውቀትና መረጃን ወደላይም ወደታችም በማሰራጨት አመራሩንና

 አባላትን ማብቃት፣ እንዲሁም ግልፅነትን በመተግበር፣ የ‹ጀርባ ፖለቲካ›ን ማዳካም ይቻላል፡፡ ይህ ሲሆን ነው ኩነቶችን ከመበለጥና
ያለመበለጥ፤ ከመሸነፍና ያለመሸነፍ አኳያ ብቻ የማየቱ አባዜ የሚለወጠው፡፡ ከእዚህ ሁሉ ስንክሳር በላይ ደግሞ በምሬቷ ብዛት
በአማራጩ ኃይል ላይ ተስፋ የጣለች ሀገር መኖሯም ከእያንዳንዷ እንቅስቃሴ ጋ መታወስ ይኖርበታል፡፡

በመጨረሻም-የአልባራዲ መንገድ

ሀገሪቱ ካለችበት ወሳኝና ታሪካው ወቅት አኳያ ቢያንስ በመንግስት ጥቁር መዝገብ ስማቸው ያልሰፈረ፣ እውቀትና አቅም ያላቸው፣
በየትኛውም ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በራሳቸው መንገድ ወደ ሀገራቸው ገብተው ትግሉን ማገዝ የሀገሪቱ ወቅታዊ ሁናቴ
የሚያስገድደው ነው፡፡ በተለይም በእንዲህ አይነት ጉዳዮች ከትምህርትም ሆነ ከመስክ ልምድ ያካበቱ ወንድምና እህቶች የግብፃዊውን
መሀመድ አልባራዲ መንገድ ቢከተሉ፣ አንድም ሁኔታዎች ከቁጥጥር እንዳይወጡ ማገዝ ይችላሉ፤ ሁለትም አብዮቱን ከሽንፈትና ቅልበሳ
ይታደጋሉ፡፡

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

Tuesday, September 24, 2013

15 የሚሆኑ የአንድነት ፖርቲ አባላት ዛሬ ህገወጥ እስር ተፈጸመባቸው

September 24th, 2013  
 
አንድነት ፓርቲ በመጪው እሁድ መስከረም 19 ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር ለሚያደርገው ሰላማዊ ሰልፍ የመኪና ላይ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ 15 አባላቱ ህገወጥ እስር ተፈፀመባቸው፡፡ አባላቱ ከስድስት ኪሎ ወደ አራት ኪሎ በሚወስደው ጎዳና በመኪና ላይ እየቀሰቀሱ ባለበት ወቅት ሚኒሊክ ት/ቤት ፊትለፊት የፖሊስና የደህንነት ኃይሎች የሚተላለፈውን መኪና መንገድ በመዝጋት ቅስቀሳውን አደናቅፈዋል፡፡

553582_717269128289551_1267195516_nበስፍራው የነበሩ በርካታ ሰዎች “ቀስቃሾቹ ህጋዊ ወረቀት ይዘዋል፤ልቀቋቸው” በማለት ተቃውሞ አሰምተዋል ከአንድነት ፓርቲ ጎን እንደሚቆሙም ተናግረዋል፡፡ ፖሊስ 15 የሚሆኑትን የቅስቀሳ ቡድን አባላት ወደ ሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋቸዋል፡፡

 የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች አባላቱ ወደ ታሰሩበት 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ በመሄድ ረ/ኢ መንግስቱ ለማ የተባሉትን የፖሊስ ጣቢያው ኃላፊ የታሰሩት አባላት እንዲለቀቁ ጠይቀዋል፡፡ ኃላፊውም “ህጋዊ ሰልፍ እንደምታደርጉ እናውቃለን ይቀስቅሱ የሚል መመሪያ አልደረሰንም ብለዋል፡፡ አመራሮቹ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነርንና የከተማዋን መስተዳድር ሃላፊዎች ለማነጋገር ተንቀሳቅሰዋል፡፡

በተለያየ አቅጣጫ የተሰማሩት ሌሎቹ የአንድነት ፓርቲ ቅስቀሳ ቡድን አባላት ስኬታማ የመኪና ላይ ቅስቀሳ በማደረግ ላይ ናቸው፡፡

በተያያዘም ዜና የአራት ኪሎ ነዋሪዎች እውቅና ተችሮታል የተባለን የአንድነት የመስከረም 19 ሰላማዊ ሰልፍ ህዝብ አሳታፊ ለማድረግ ዛሬ ማለዳ ከአንድነት ቢሮ በዛ ያሉ መኪኖች ለቅስቀሳ ወጥተዋል፡፡

በአራት ኪሎና በአካባቢዋ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንን ለመቀስቀስ ከወጡ መኪኖች መካከል የተወሰኑት በፖሊስ በህገ ወጥ መንገድ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርገዋል፡፡
በመኪኖቹ ውስጥ የነበሩትን የአንድነት አባላት ፖሊስ ወደ ጣብያ ለመውሰድ ባደረገው ሙከራ ህዝብ መሰብሰብ ችሏል፡፡ሁኔታውን በአንክሮ ይከታተል የነበረ ህዝብ ፖሊሶቹን ልጆቹን መውሰድ አትችሉም፣ሰልፉ እንደተፈቀደ እየታወቀ መቀስቀስ አትችሉም ማለታችሁ ህገ ወጥ ድርጊት ነው››በማለት እጅግ በሚያስደስት ሁኔታ ተከራክረዋል፡፡

አዎን ህገ ወጥ ድርጊት ሲፈጸም በእኔ ላይ ካልሆነ ምን አገባኝ ብለን የምናልፍበት ዘመን ማብቃት ይኖርበታል ፡፡ይህንን ደግሞ የአራት ኪሎ ሰዎች ስለ ጀመሩት ከወዲሁ ምስጋናችን ይድረሳቸው፡፡

የአባይ ቡድን በሁለት ተከፈለ!

September 24/ 2013

ህወሓት በአባይ ወልዱና ደብረፅዮን ቡድኖች በሁለት መከፈሉ ይታወቃል። ባለፈው የህወሓት የማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ የአባይና የደብረፅዮን ጠብ በጣም በመክረሩ የተነሳ ሽጉጥ መማዘዛቸው ተሰምቷል። ሃይለማርያም ደሳለኝና በረከት ስምዖን ለማስታረቅ የሞከሩ ሲሆን ዉጤቱ አልታወቅም። ይህ በንዲህ እንዳለ የአባይ ቡድንም ሰሞኑ በሁለት ተከፍሏል፤ የአባይ ወልዱና የበየነ መክሩ። ከህወሓት ስብሰባ በኋላ የስልጣን ሽግሽግ ለማድረግ የተሞከረ ቢሆንም በየነ መክሩና ኪሮስ ቢተው ከስልጣናቸው ለመውረድ (ሓላፊነት ለመቀየር) ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ከአባይ ወልዱ ጋር ከፍተኛ አምባጓሮ ተፈጥሯል።


ኪሮስ ቢተው የግብርና ቢሮ ሓላፊና የኢንተርፕራይዞች የቦርድ ሰብሳቢ ነበር። አባይ ወደ ሌላ ቢሮ ሊቀይሮው አስቦ ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል። የኢንተርፕራይዞች (ብዙ በጀት የሚመደብበት) ስልጣን ግን ቀምቶ ለአለም ገብረዋህድ ሰጥቶታል። ግብርና ቢሮም ለወደ አዳል ታስቦ ነበር። ግን ጠብ ስለተነሳ አልተሳካም። በየነ መክሩም የንግድና ኢንዱስትሪ (የከተማ ልማት ጨምሮ) ስልጣን በእጁ ሲሆን አባይ ቢሮው ለሌላ ሊሰጠው ፈልጎ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ግን እስካሁን ውዝግብ ላይ ናቸው። በየነ መክሩ ወደ ሀገሩ (እስራኤል) የመሄድ ሓሳብ ይዟል።
የአባይ ቡድን በሁለት መከፈሉ (አባይና በየነ የሚመሩት) ማሳያ በትግራይ ክልል የዉሃ ሃብት ቢሮ አመራር አባላት የሁለቱ ቡድኖች ደጋፊዎች ተጣልተው እንደተደባደቡና አከባቢው እስካሁን በፌደራል ፖሊስ እየተጠበቀ መሆኑ ተረጋግጧል።
ስርዓት ሲበሰብስ እንዲህ ነው። ለማንኛውም ቸር ያሰማን።

ወያኔ በባሕርይው ጅብና ውሻ ነው::

January5 24/ 2014
አውሬ አውሬነቱን አይረሳም” አለ ልበል ተወልደ (ተቦርነ) ስለአንበሣው ቀላቢውን መግደል ሲያወራ አሁን? አዎ፣ ብሏል፡፡ እውነት ነው ፤ አውሬ አውሬነቱን አይረሳም፡፡ ወያኔም ወያኔነቱን አይረሳም – እባብ የትምና መቼም ቢሆን እባብነቱንና የወጣበትን ጉድጓድ እንደማይረሣ ሁሉ፡፡ ወያኔ ፀረ-ኢትዮጵያ ነው፤ ወያኔ ፀረ-አማራ ነው፤ ወያኔ ፀረ-ሃይማኖት ነው፤ ወያኔ ፀረ-ሰላምና ፀረ-ዴምክራሲ ነው፡፡ ወያኔ ኢትዮጵያንና ትውፊቶቿን ለማጥፋት የተነሱ የውጭ ኃይላት ብቸኛ ወኪል ነው - ‹የአድኅሮት ኃይላት ተላላኪ፣ የኢምፔሪያሊዝምና የቢሮክራሲያዊ ካፒታሊዝም አራማጅ ቅጥረኛ› ልበልና የደርግን ዘመን አብዮታዊ ትዝታ ልቀስቅስባችሁ ይሆን? ወያኔ እነኚህን መሰሎቹን የተፈጥሮ ሣይሆን የተጋቦት ባሕርያቱን መቼም አይረሳም - ቢጠግብም - ቢወፍርም -አገርና አካባቢ ቢለውጥም - እርስ በርሱ ቢጣላም - በሎሚ ተራ ተራ አንዱ አንዱን ቢያስርና ቢገርፍም - በማንኛውም ረገድ ወያኔ የተነሣበትን የወያኔነት ጠባይና ምግባሩን አይረሳም፡፡

 በዚያ ላይ ደግሞ ሰውን ጨምሮ በብዙ እንስሳት የማይታይ አንድ እጅግ አስገራሚ ጠባይ አለው፤ ያም “አህያ ለአህያ ቢራገጥ ጥርስ አይሳበርም” እንዲሉ በወያኔዎች መካከል ደም እስከመቃባት የደረሰ ጠብና ቅራኔ በነሣም እንደቃል ኪዳን ሆኖ ወያኔ ወያኔን ለሌላ አካል አጋልጦ የማይሠጥ መሆኑ ነው፤ ለዚህም ነው አቶ ስዬ አብርሃ ለአሳሪው ለአቶ መለስ ዜናዊ ሞት ፍራሽ አንጥፎ ከነቤተሰቡ ልቅሶ ተቀምጦ እንደነበር መስማት የቻልነው - መቼም ስዬ እንደክርስቶስ መሓሪ ወይም እንደእግዚአብሔር ሁሉን ታጋሽና ቻይ ሆኖ ነው ብንል ራሱ ስዬ ይታዘበናል - ይህ አስገራሚ ክስተት ከዘረኝነትና ከጎጠኝነትጋር የተያያዘ መሆን አለበት፡፡ ይቅርታ ይደረግልኝና ያን ሁሉ ግፍና በደል በኔና በቤተሰቤ ያደረሰብኝ ደብረታቦሬ የ‹ሀገር መሪ› ቢሞት ከሞራልና ከሃይማኖት እንዲሁም ከባህል አንጻር በደስታ ጮቤ መርገጡ ቢቀርብኝ ማቅ መልበሱና ሀዘን መቀመጡ ግን በሟቹ የመቀለድ ያህል እንደሚያስመስልብኝ እገምታለሁና የምሞክረው አይመስለኝም፡፡ የነእንትና ነገር ግን ‹አታሃዛዚቡና› እንደተባለው ነው፡፡ እያልኩ ያለሁት በመለስም ሆነ በሌሎች ወያኔዎች የተበደሉ ወያኔዎች አይዘኑ አይደለም፡፡ ከፈለጉ ቅጥ ባለው መንገድ ማዘን ይችላሉ፤ በይሉኝታቢስነታቸው ቀጥለውበት ትዝብት ውስጥ መግባትን ከቁብ ካልጣፉት ደግሞ ፊታቸውን መንጨትና ሰባትም ዐሥራ አራትም ዓመት ከል መልበስ ይችላሉ፡፡ መጠቆም የፈለግሁት የነሱን ጠብ በውኃ እንደሚፀዳ ተራ ነገር የሚቆጥሩ ሲሆኑ፣ በሌሎች ላይ ቂምና የነገር ቁርሾ ከቋጠሩ ግን ባላጋራዎቻችን ናቸው ብለው የፈረጇቸውን ዕድለቢስ  ወገኖች መቀመቅ ካላስገቡ በቀላሉ የማይለቁ እጅግ ሲበዛ መርዘኛ መሆናቸውን ነው፡፡  


አለመለከፍ ማለት ቀድሞውን ወያኔን አለመሆን ወይም ወያኔን ሆኖ አለመፈጠር ነው እንጂ አንዴውኑ በወያኔነት ልምሻ ከተኮደኮዱ በኋላ የፈውሱ ነገር አዳጋች ነው - በተለይ እንዳሁኑ ዘመን ጊዜ እየነጎደ በሄደ መጠን የተፈጠሩበትን ዕለት እስከመራገም ለሚያደርስ አሰቃቂ የመጨረሻ ዕጣ ይዳርጋል፡፡ ከዚህ ከወያኔው ዓይነት የዘረኝነት ልክፍት የሚፈወሱና ጤነኛ ሰው የሚሆኑ - ጤነኛ ሆነውም አውቀው አምነውበትም ይሁን ሳያውቁ ተታልለው የበደሉትን ሀገርና ሕዝብ ለመካስ የሚተጉ እጅግ ጥቂቶች ናቸው - ያም እንደገና የመወለድ ያህል መታደል ነው - ለነሱም ለሀገርም፡፡ እንደነዚህ ዓይነት ሰዎች ደግሞ የዕንቁ ያህል ውድ ናቸው፤ በቀላሉና የትም አናገኛቸውም፡፡ እናም እንግባባ - ወያኔ ወያኔነትን የትም ሆኖና በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ሆኖ  ለአፍታም አይዘነጋትም፡፡ መዘንጋት ለኅልውናው አደጋ እንደሆነ ያህል ስለሚቆጥረው ይመስለኛል፡፡ አንዲት ማረሚያ ቤት የምትገኝ  የወያኔ ወታደር ከዚህ በፊት በጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ላይ ፈጸመችው የተባለው አስነዋሪ የዘረኝነት ድርጊትም ከዚህ ጋር በቀጥታ የሚገናኝ ነው - ለዚህች ደንቆሮ ‹እሥረኛ› ወያኔነት ማለት የገነትም የመንግሥተ ሰማይም ገዢ ነው - ‹እሥር ቤቱና አሣሪዎቹ እኛው እስከሆን ድረስ፣ ገዢዎቹ እኛው እስከሆን ድረስ ይበልጥ እሥረኛ ሌሎች እንጂ እኛ አይደለንም› ብላ ሳታምን አልቀረችም(ይህ ዓይነቱ ከፍተኛ ሞኝነት የሚነበብበት የወያኔዎች አካሄድ የጆርጅ ኦርዌልን “All animals are equal, but some animals are more equal than the others.” የሚለውን ያስታውሰኛል፡፡) የብዙዎቹ ወያኔዎች መርሆ  እነዚህ ብሂሎች ልብ እንድንል ያደርጉናል፡- “የዘሬን ብተው ያንዘርዝረኝ”፣ “ትንሽ ሥጋ እንደመርፌ ትወጋ” ፤ “የሥጋ ትል የዘመድ ጥል” ፣ በእንግሊዝኛው ደግሞ  “Blood is thicker than water.”  ይህ የወያዎች ‹የዋህነት› የሚያሳየን ግን የእግዚአብሔርን መንገድና ትክክለኛውን ማኅበረሰብኣዊ የዕድገት ደረጃን ሣይሆን በዝቅተኛ የንቃትና የዕውቀት ደረጃ የሚገኙ የሌሎች እንስሳትን ነሲባዊ የመሳሳብ ጠባይ ነው፡፡ ሰው ከሰውነት ደረጃ ወርዶ እንዲህ ያለ የደምና የአጥንት ማነፍነፍ ቅሌት ውስጥ ሲገባ ማየት ደግሞ በማኅበረሰብም ይሁን በሀገር ደረጃ ከፍተኛ አለመታደልና የሀፍረት ምንጭም ነው፡፡
የተወልደ በየነ ንግግር እንደዐረብ ጣቢያ ድንገት ጣልቃ ገብቶብኝ በርሱ አባባል ጀመርኩ እንጂ አነሳሴ ቲቪ እያየሁ ሳለ በተጓዳኝ እያነበብኩት በነበረውና አሁን በጨረስኩት አንድ ድንቅ መጣጥፍ ላይ ተመርኩዤ የበኩሌን ጥቂት ለማት ነበረ፡፡ ይህን መጣጥፍ ያገኘሁት በዘሀበሻ ድረ ገጽ ላይ ነው - በፒዲኤፍ የቀረበና ከሰሞነኛ መጣጥፎች ቀልቤን ክፉኛ የሳበ ቆንጆ ጽሑፍ ነው፡፡ ይህ ግሩም ጽሑፍ የቀረበው ከአንድ በስደት ላይ እንደሚገኝ የገለጸ የቀድሞ የመንግሥት ሚዲያ ዘጋቢና የኮሚኒኬሽን ባለሙያ ነው፡፡ ጽሑፉ የሚያትተው ወደፊት መጽሐፍ ሆኖ ይወጣል ከተባለና አንድ የወያኔ ከፍተኛ ባለሥልጣን ይሄው የመንግሥት ሚዲያ ዘጋቢ ከሀገር ሊወጣ ሲል  ለሰባት ሰዓታት ያህል በመቅረፀ ድምጽ አጋዥነት ሰጠው ከተባለው የኑዛዜ ቃል ተቀንጭቦ የቀረበ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ ርዕሱ “በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ ከሚገኝ የልብ ወዳጄ ጋር በአገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያደረግሁት ምሥጢራዊ ውይይት” ይላል፡፡ ትንሽ ረዘም ቢልም መነበብ ያለበት ማለፊያ ጽሑፍ ነውና እባካችሁ አንብቡት - ሀገር በጣር ላይ እያለች ለማንበብ መድከም የለብንም፡፡ በተፋፋመ ጦርነት ውስጥ ገብቶ ለሀገር መዋደቅስ አለ አይደል? እየቀነጨብኩ ለፈርጥ ያህል በዚች መጣጥፍ ውስጥ በመጠኑ እንዳልጠቅስላችሁ ጽሑፉን ከፒዲኤፍ ወደወርድ ስለውጠው አንዳንድ ሆሄያት ቅርጻቸው እየተንሻፈፈብኝ ተቸገርኩ፡፡ ወያኔ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚተገብራቸውን ሥልቶች ብዙዎቹን ታገኙበታላችሁ፡፡ ወያኔ የቱን ተመርኩዞ የቱን እንደሚያጠፋና ቀጥሎም አንዱን ለማጥፋት የተጠቀመበትን ምርኩዝ ሰባብሮ የትም እንደሚጥል - ባጭሩ ሕወሓት አስብቶ አራጅ መሆኑን ትረዱበታላችሁ›፡፡ በምታምኑት ይሁንባችሁና ግዴላችሁም አንብቡት!
ወያኔ በባሕርይው እንደጅብም፣ እንደውሻም፣ እንደዓሣማም፣ እንደእስስትም፣ እንደእባብም … ነው፡፡ ለወያኔ የባሕርይ መግለጫነት የማይሆኑ ርግብን የመሳሰሉ የዋሃን ፍጡራን ብቻ ናቸው፡፡ በተረፈ ወያኔ ማለት የክፋት ተምሳሌት የሆኑ የተፈጥሮም ይሁኑ ሰው ሠራሽ ነገሮች ውሁድ ሥሪት ነው፡፡ የክፋት አድማሱ ደግሞ ወሰን የለውም፡፡ ድንበር የለሽ ክፋት ደግሞ ድንበርን ተሻግሮ ብዙ ዘመናትን የማጣቀስ ጠባይ አለው፡፡ ለዚህ ነው የክፋት አምባሳደሩ ወያኔም ሞተ ሲሉት እየተነሳ በአፈ ታሪክ ዘጠኝ ነፍስ ያላት መሆኗ እንደሚወራላት ድመት እስካሁኒቷ ቅጽበት ድረስ በአፀደ ሕይወት ሊገኝ የቻለው፡፡
የወያኔ ውሻዊ ባሕርይ፡፡ ውሾች እርስ በርስ ሊዋደዱም ላይዋደዱም ይችላሉ፡፡ ግን ግን እነሱም ልክ እንደብዙዎቹ እንስሳት ዘር መንጣሪና ከ”species”ኣቸው ውጪ ከሌሎች ጋር እምብዝም አይቀላቀሉምና በአደንም ሆነ በሥሮት ወቅት  አይለያዩም፡፡ ወያኔዎች ከውሻ የወሰዱት ጠባይ ታዲያ ውሾች በግላቸው የፈለጉትን ያህል ይጣላሉ፣ ይነካከሳሉም እንጂ የውጪ ጠላትና የአደጋ ሥጋት ከተደቀነባቸው ቂጣቸውን ይገጥሙና ያን ጠላት በጋራ ይከላከላሉ፤ በክፉ ቀን በመካከላቸው ንፋስ አይገባም፡፡ አጥንት ላይ የተፋጠጡና የሰገሌን ጦርነት በውሻኛ “version” ሊደግሙት የተዘጋጁ ውሾች ሳይቀሩ ያን ሆድ-ተኮር ጠብ በጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት አቁመው የመጣባቸውን የጋራ ጠላት በጋራ ይጋፈጣሉ፤ በውነቱ ይህ መልካም ጠባይ ነው፡፡ በወያኔዎች ላይ ብቻ ተወስኖ መቅረቱና በሰባና ሰማንያ ሚሊዮን በሚገመተው አጠቃላዩ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲሁም በሌሎች የፖለቲካና ማኅበረሰብኣዊ ስብስቦች ዘንድ አለመሥራቱ ግን ያሳዝናል፤ ይቆጭማል፡፡ እነሱ ብልጥ ሲሆኑ ሌላው ጅላንፎ ሆኖ እስከወዲያናው በሚመስል ሁኔታ ሲጃጃል መታዘብ ትልቅ ቁጭት ነው፡፡ ከውሻ እንኳን መማር ያቃታቸው ኢትዮጵያውያን ተቃዋሚዎች ወያኔ በቀደዳለቸው የልዩነት መስመር እየተመሙ ለወያኔው ዕድሜ መራዘም ጠንክረው በመሥራት ላይ ይገኛሉ፡፡ መቼ ነፍስ እንደሚያውቁና ለከርታታው ‹ሕዝባቸው› መሢሕነታቸውን እንደሚያሳዩ አናውቅም፡፡ ውሻ በበጎም ሆነ በክፉ ብዙ ተጠቃሽ ባሕርያት ቢኖሩትም ለጊዜው ይህ በቂየ ነው፡፡
የወያኔ ጅባዊ ጠባይ፡፡ ጅብ ፈሪ ነው፡- ወያኔም በጣም ፈሪ ነው፡፡ ገደልኩት ብሎ የሚያምነውን ‹ጠላቱን› እንኳን የሚፈራና መቃብር ውስጥም ገብቶ ዐፅምን በምናባዊ የስድብና የምፀት ጅራፍ የሚገርፍ፣ በሙታንም ላይ የሚሣለቅና የሚቀልድ ነው - ወያኔ፡፡ ለምሳሌ አማራንና ኦርቶዶክስን ገድሎ እንደቀበራቸው በወያኔዊ መድረኮች ካላንዳች ሀፍረትና ይሉኝታ እየተደሰኮረ ነው፡፡ ግዴለም ሞቱ እንበል፡፡ በሕይወት ያሉ እየመሰለው ታዲያን በባነነ ቁጥር በሚናገራቸው የዕብሪት ቃላቱና በሚያከናውናቸው ፀረ-ሕዝብ ተግባራቱ  ለትዝብት እንደተዳረገ አለ ፡፡ ፍርሀት በራስ የመተማመን ችሎታን ያሳጣል፤ ፍርሀት ቤቱን የሠራበት ሰው እንደመለስ ተሳዳቢና አሽሟጣጭ ይሆናል፡፡ ፍርሀት ያሸነፉትን ጠላት እንዳላሸነፉት በማስቆጠር ቀን በእውን ሌት በውን እያስባተተና እያስቃዠ ወንጀለኛና ኃጢኣተኛ ያደርጋል፡፡ የወያኔ ወንጀል እየተቆለለ ሄዶ ለፍርድ አስቸጋሪ እስኪሆንበት ድረስ ፈጣሪን እያስጨነቀ ያለው እንግዲህ ከዚህ መሠረታዊ ምክንያት በመነጨ መሆን አለበት፡፡ እንዲያ ባይሆንስ ቁናው ከሞላ ሰንብቷል፡፡
ጅብ ሆዳም ነው፡፡ የጅብ ሆድ ደግሞ የሚመርጠው የለም፡፡ ያገኘውን እየሰለቀጠ ወደጎሬው ይገባል፡፡ የነጋበት ጅብ በተለይ አይጣል ነው፡፡ ወያኔ እንደዛሬው ሳይነጋበትም ሆነ እንደዱሮው በጊዜ ያገኘውን ሁሉ ማግበስበስ መነሻና መድረሻ ዋና ጠባዩ ነው፡፡ ወያኔ አይጠግብም - እምብርት የለውምና፡፡ ከመሰል ሰብኣዊ ጅቦች ጋር ሆኖ ኢትዮጵያን ራቁቷን እያስቀራት ያለ ወያኔ ነው፡፡ ጅብ ሆዳም ብቻ አይደለም፡፡ የብዙ ብልሹ ምግባራት ተምሳሌት ነው፡፡ ለአብነት እርስ በርሱ አይተማመንም፡፡ ከዚያም የተነሣ ሲሄድ እንኳን ፊትና ኋላ ሆኖ ሳይሆን ጎን ለጎን ሆኖ ነው ይባላል፤ በተለይ የቆሰለ ጅብ በመንጋው ውስጥ ካለ በጣም ካልተጠነቀቀ በስተቀር ከአህያ ያልተናነሰ ዕድል እንደሚገጥመው ይነገራል - በቁሙ ነው አሉ እሚዘረጥጡት፡፡ ወያኔም እንደዚሁ ነው፡፡ አይተማመኑም፤ እርስ በርስ ይበላላሉ፡፡ ተባልተው ተባልተው መጨረሻቸው ደርሷል እየተባለ ነው አሁን፡፡ ለሰው ማን እንዲህ ሹክ እንደሚለው አላውቅም፤ ግን ‹መዥገሩ ወያኔ በደም አብጦና በደም ሰክሮ ሊፈርጥና ሊበታተን ነው› እየተባለ በየቦታው ሲወራ እሰማለሁ - ወፍ ትሆናለች እንዲህ እያለች ምሥጢር እያወጣች ያለች - እንዳፏ ያድርግልን፡፡ ለመሆኑ ግና - መለስ ብለን መለስን ስናስታውስ የወዲ ዜናዊ ሠይፍ ያልቀላው ትላልቅና ትናንሽ ወያኔ አለ ወይ? እንዴ፣ ያልተቆረጠመ ሰው እኮ የለም፤ የመለስ ነዲድና ፍላጻ ሞኛሞኙንና ቅን ታዛዡን ብቻ መርጦ ትቷል፡፡ በልዩ ወርቃማ ዕድል ከዐይኑ የተሠወሩበት ጥቂት ብልጣብልጦችና አድርባዮች ለዘር እንዲተርፉ የመለስ ውቃቢ አምላክ ምሯቸው እንደሆነ እንጂ መለስ የፈጀው ሕዝብ እኮ በውነቱ ከግምት በላይ ነው፤ መለስ ዜናዊ? ኧሯ! በጊዜ መሰብሰቡ በጄ(ን/-ኣቸው(?)) እንጂ ከርሱ ሾተል ማን ሊተርፍ ይቻለው ነበር? በተለይ እሱ የወያኔ ባለሥልጣን ከሆነበት የብረት ትግሉ የመጀመሪያ ዓመታት ጀምሮ በዚህ ሰውዬ ሥውርና ግልጽ ትዕዛዝ እንዲሁም የሽርና የተንኮል ሤራ በመርዝና በጥይት ብዙ የወያኔ ታጋይ እንዳለቀ ለጉዳዩ ቅርበት ባላቸው ሃቀኛ ወገኖች የተጻፉ ድርሳናት ይመሰክራሉ - የገብረ መድኅን አርአያ ጽሑፎችን ያነቧል፡፡ ይሄ ሁሉ እየታወቀ ግን መለስን እስከማምለክ ተደርሷል - ምክንያቱም መለስን መቃወምና መንቀፍ ማለት ከጥቅምና ከጋርዮሽ ዘውጋዊ ቁርኝት ጋር ይጣረሳላ! ምክንያቱም መለስን መቃወም ማለት አሁን የተደረሰበትን የአንድ ብሔር ሸፋፋና ቅጥየለሽ “የበላይነት” ሊያሳጣ እንደሚችል ይታመናላ! ድንቄም የበላይነት! የበላይ የሆኑትስ እየተበደሉና እየተረገጡ የሚገኙት በርካታ ሚሊዮን ወገኖች ናቸው፡፡ የበላይ የሆኑትስ እየተራቡና እየተጠሙ፣ እየታረዙና እየታመሙ፣ እየተጋዙና እየተገደሉ፣ በእሥርና በስደት አሰቃቂ ሕይወትም መከራቸውን እየበሉ ያሉት ምሥኪኖች ናቸው፡፡ የበላይ የሆኑትስ በገዛ ሀገራቸው እንደሦስተኛና አራተኛ ዜጋ ተቆጥረው የማንኛውም የኢኮኖሚና የፖለቲካ መብታቸው ሳይከበርላቸው እንደከብት እንዲኖሩ የተገደዱ ትግሬውን ጨምሮ የየትኛውም ዘውግ አባላት ናቸው፡፡ የበላይ የሆኑትስ ለኅሊናቸው ያደሩና ሀገራቸውን ከወያኔ ጋር ተባብረው ያልሸጡ የሁሉም ዘውግ አባላት ወገኖቻችን ናቸው፡፡ ማን የበላይ ማን ደግሞ የበታች እንደሆነ በጊዜ ሂደት የምናየው ይሆናል፡፡ በጮማ ግሣትና በውስኪ ብስናት ሕዝብ ላይ እያቀረሹ መኖር የበላይነት መገለጫ ሳይሆን የአውሬነትና የእንስሳነት ጠባይ ማሳያ ነው፡፡ ኤዲያ … በቃኝ እባክሽ፤ አናጋሪዎች!