Monday, July 22, 2013

በወረባቡ የአንድነት አባላትን ጨምሮ 45 ወጣቶች ታስረዋል

በደቡብ ወሎ ዞን በረባቡ ወረዳ በስግደት ላይ የነበሩ የአንድነት ፓርቲ አባል የሆኑት አቶ አብዱ መሐመድ እና አቶ እንድሪስ አህመድን ጨምሮ 45 ወጣቶች መታሰራቸውን ምንጮቻችን ከስፍራው በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡

ከታሰሩት መካከልም ወጣት ሱልጣን መሐመድ በከፍተኛ ህመም እየተሰቃየ እንደሚገኝና እስካሁንም የህክምና እርዳታ እንዳልተደረገለት ተጠቁሟል፡፡ መንግስት የወረዳውን ነዋሪዎች የደሴው ሼህ ኑሩ ይማምን መገደል በሰላማዊ ሰልፍ ካላወገዛችሁ የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ አይሰጣችሁም፣ ዘርና ማዳበሪያም አታገኙም የሚል ማስፈራሪያ በካድሬዎች አማካኝነት እየተሰጠ መሆኑንም ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡
በተለይ ከታሰሩት 45 ወጣቶች መካከል 3ቱ ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች በመሆኑ የእድሜ ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሆነ እና ወጣቶቹ ከመስኪድ ውጭ በአካባቢው ሜዳ ላይ ሲሰግዱ ስለተወሰዱ አብዛኞቹ ቤተሰቦቻቸው እንደማያውቁና እስካሁንም እየፈለጓቸው መሆኑ ታውቋ፡፡ ወጣቶቹም ከታሰሩ ከሳምንት በላይ የሆናቸው ሲሆኑ እስካሁን ክስ እንዳልተመሰረተባቸው ተጠቁሟል፡፡ ይህን ዜና እስክናሰራጭ ድረስ ከታሳሪዎች መካከል  ከፊሉ በደሴ ቀሪዎቹ ደግሞ በሐይቅ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ እስር ላይ እንደሚገኙ የደረሰን መረጃ አመልክቷል፡፡ የዝግጅት ክፍሉም ከወረዳውና ከደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደርና የፀጥታ ክፍል ስለጉዳዩ ለማጣራት ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም አልተሳካም፡፡

በደቡብ ወሎ ዞን በረባቡ ወረዳ በስግደት ላይ የነበሩ የአንድነት ፓርቲ አባል የሆኑት አቶ አብዱ መሐመድ እና አቶ እንድሪስ አህመድን ጨምሮ 45 ወጣቶች መታሰራቸውን ምንጮቻችን ከስፍራው በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡
ከታሰሩት መካከልም ወጣት ሱልጣን መሐመድ በከፍተኛ ህመም እየተሰቃየ እንደሚገኝና እስካሁንም የህክምና እርዳታ እንዳልተደረገለት ተጠቁሟል፡፡ መንግስት የወረዳውን ነዋሪዎች የደሴው ሼህ ኑሩ ይማምን መገደል በሰላማዊ ሰልፍ ካላወገዛችሁ የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ አይሰጣችሁም፣ ዘርና ማዳበሪያም አታገኙም የሚል ማስፈራሪያ በካድሬዎች አማካኝነት እየተሰጠ መሆኑንም ምንጮቻችን ገልፀዋል፡

በተለይ ከታሰሩት 45 ወጣቶች መካከል 3ቱ ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች በመሆኑ የእድሜ ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሆነ እና ወጣቶቹ ከመስኪድ ውጭ በአካባቢው ሜዳ ላይ ሲሰግዱ ስለተወሰዱ አብዛኞቹ ቤተሰቦቻቸው እንደማያውቁና እስካሁንም እየፈለጓቸው መሆኑ ታውቋ፡፡ ወጣቶቹም ከታሰሩ ከሳምንት በላይ የሆናቸው ሲሆኑ እስካሁን ክስ እንዳልተመሰረተባቸው ተጠቁሟል፡፡ ይህን ዜና እስክናሰራጭ ድረስ ከታሳሪዎች መካከል  ከፊሉ በደሴ ቀሪዎቹ ደግሞ በሐይቅ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ እስር ላይ እንደሚገኙ የደረሰን መረጃ አመልክቷል፡፡ የዝግጅት ክፍሉም ከወረዳውና ከደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደርና የፀጥታ ክፍል ስለጉዳዩ ለማጣራት ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም አልተሳካም፡፡

- See more at: http://www.fnotenetsanet.

No comments: