Friday, July 26, 2013

ፒያሳ የሙስሊም ኢትዮጵያውያንን የተቃውሞ ድምጾች አስተናግዳ ዋለች

ሐምሌ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ፒያሳ ከሚገኘው ኑር መስጊድ አንስቶ ዙሪያውን ባሉ መንገዶች ላይ ቆሞ የረመዳንን ጁመዓ ስግደት ሲሰግድ  የዋለው ሙስሊሙ ኢትዮጵያዊ ፣ ከአንድ አመት በላይ ሲያሰማው ነበረውን ድምጻችን ይሰማ የሚለውን ተቃውሞ በከፍተኛ ድምጽ በማሰማት የፒያሳን አየር ተቆጣጥሮት ውሎአል።

ድምጻችን ይሰማ፣ የተነጠቅነውን መስጂዶቻችን ለህዝቡ ይመለሱ፣ የተባረሩ ኢማሞች ይመለሱ፣ አሸባሪ አይደለንም፣ ኢማሞቻችን ይፈቱ፣ ጥያቄው ይመለስ፣ ህገ መንግስቱ ይከበር፣ መጅሊሱ አይወክለንም የሚሉትና ሌሎችም ጥያቄዎች ቀርበዋል።
የዛሬው ተቃውሞ ከአንዋር መስጊድ መውጣቱ ብቻ ሳይሆን በተቃውሞው ላይ የታየው የህዝብ ብዛትና የተሰማው ድምጽ ህዝብን ትኩረት ስቦአል።

ተቃውሞው ከአዲስ አበባ ውጭ በተለይም በሻሻመኔ የፌደራል ፖሊሶች  በብዛት በተገኙበት ሁኔታ ተካሂዷል።
መንግስት የሙስሊሙን  ጥያቄ የጥቂቶች ጥያቄ ነው ቢልም በተለያዩ አካባቢዎች በገሀድ የሚታየው እውነታ ይህን የሚያረጋግጥ አልሆነም።

የኢትዮጵያ መንግስት ሙስሊሙ ለሚያቀርበው ጥያቄ እስካሁን ድረስ ተገቢውን መልስ አልሰጠም።

No comments: