Sunday, July 21, 2013

አሸባሪዉ ኢህአዴግና የፀረሽብር ህጉ መወገድ አለባቸዉ

July 21/2013

ኢትዮጵያንና ህዝቧን የአብሮነትን መሠረት  እና ፍቅር ለመሸርሸርና ብሎም ለማጥፋት ሌተ ቀን የማይተኛዉ የህወሀት የወያኔው የወያኔው አሸባሪ መራሹ መንግስት በህዝብ ጫንቃ ላይ ተቀምጦ የኢትዮጵያን ሀብት እና ንብረት እየዘረፈ የሕዝባችንን ደም እየመጠጠ እና ዜጎችን ማሰቃየት ከጀመረ እነሆ 22 አመት ተቆጥሮዋል። 

 ነገር ግን የ22 አመት ቆይታዉ ህዠብን  እና ንጹሐነን ዜጓቸ ከማሸበር፣ ከመግደል፣ ለመብታቸው እና ለህዝብ ነጻነት የቆሙትን እውነተኛ ጋዚጠኞችን እና የፖለቲካ ሰዎችን ከማሰር ከማሰደድ፣ከመግረፍና ከማፈናቀል አልፎ በተመቸዉና የጥፋት ምርቃናዉ በመጣለት ቁጥር በዘረኞች መሪዎቹ አማካይነት በፈለገዉ ሰዐት ከራሱ ህግና ስርአት  ውጪ ከእንቅልፋ እንደሚነቃና የሚያደርገዉን እንደማያቅ ህፃን ልጅ የተለያዮ ህጎችን በማዉጣት ጭምርህዝባችንን ከህዝባችን እንዲሁም ሀገሪቱዋን ባለቤት የሚያሳጣ አስነዋሪ ህጎች በማርቀቅና ድራማ በመስራት ማፍያ ስርአት መሆኑ ይታወቃል።  ከእነዚህ የህወሀት ኢህአዴግ አስነዋሪ ህጎች አንዱ የፀረ ሽብሩ ህግ አዋጁ በሙዋቹ ቀንደኛ ማፍያ መሪያቸዉ መለስ ዜናዊ መሪነትና በሌሎች አጭበርባሪ ሆዳም የሀገር ፍቅር በሌላቸዉ ተከታዮችአማካይነት የፀረ ሽብር ህግ አዉጥቶ አምስት መቶ አርባ አንድ  እጅ በሚያነሱለት የፓርላማ  የወያኔ አሻንጉሊቶቹ ድጋፍ ማፀደቁ የሚታወቅ ነዉ አሳዛኝ ድርጊት ነው ።

ይህ ህግ አሁንም አንባ ገነን በነበረው መሪያቸዉ የሙት መንፈስ ራእይ ስምና አሁንም በተተካዉ አሻንጉሊት በሙት መንፈስ በሚመራው  ሀይለማርያም ደሳለኝ ህጉ እንደቀጠለ ሲሆን ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚያሸብረ ወያኔ ሆኖ ሳለ ነገር ግንበመሣርያ የበላይነት በሀገሪቷ ዉስጥ ከወያኔ የተለየ ሀሳብ ያላቸዉ በህጉ የስቃይ ሰለባ እየሆኑ ነዉ በየቦታውም እየተሰቃዩ ነው ።

          ለዚህም ማስረጃ ሰሞኑን ወገናችን አንድ ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ በአንድነት ፓርቲ ጽህፈት ቤት ዉስጥ የሚሊዮኖች ድምፅ በሚል በሰጠዉ ቃለ ምልልስ ለሃያ ሶስት ወራት፣ ለሶስት ወር ማዕከላዊ ለ19 ወር ደ ግሞ በዝዋይ እስር ቤት በወያኔ ካድሬዎች በግፍ ኢሰብአዊና በረመኔያዊ የጭካኔ በደል እየቀጠቀጡ እና እየደበደቡ ፍዳዉን አብልተዉ የቁም ሞት ገለዉ ከለቀቁት በዉኃላ በዚህ የፀረ ሽብር ህግ ምክንያት ህይወቱ ጉዳና ላይ ወድቋል ንፁሀን ዜጎች ከሱ ጭምር የህጉ ሠለባ መሆናቸዉን ከአንደበቱ ሰምተናል።

          ስለዚህ ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት ዛሬ ነገ ሳይል እንደ ተስፋዬ ተካልኝ እይነት ሚሊዮኖችን  በየቦታው ከተለያዮ ግልፅና ስዉር የማሰቃያ ቦታዎች ሊታደጋቸዉ እንዲሁም አሸባሪዉ ህወሀት ወያኔ  ፀረ ሽብር ህጉን ከኢትዮጵያ ማስወገድ አለበት። አሸባሪው እሱ እራሱ ወያኔ ስለሆነ መወገድ አለበት ምክንያቱም ህዘባችን በህዚ ሽብርተኛ ህጉ መሰረት በእየቦታው እየተሰቃየ ነው :: 

       ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ   

No comments: