Sunday, July 28, 2013



2012-03-02t171851z_319859376_gm1e83303nh01_rtrmadp_3_kenyaትዝታ ዘ ባንዲራ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዘቀዘቁት ባንዲራ
ትላንት በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ላይ ኢቲቪ አንድ ግለሰብ የሆነ ነገር ሲያውለበልብ አሳየንናተቃዋሚዎቹ  ለባንዲራ የሚሰጠውን ክብር በማንቋሸሽ የተቀዳደደ ባንዲራ ሲያውለበልቡ ነበር ብሎ አሳየን… 1ኛ … ያ ሰውዬ የተቃዋሚዎቹ ተወካይ ስለመሆኑ ምንም ማስረጃ የለም፡፡ 2ኛ የያዘው ነገር ባንዲራ ስለመሆኑም መለየት አልተቻለኝም… የሆነ ሆኖ… ይቺ ዜና ወሬ ከየት ትዝ እንዳለችኝ እንጃላቷ…  ድጋሚ አትሜያታለሁ….

ጤና ይስጥልጅ ወዳጄ እንዴት አሉልኝ። ጤና ኑሮ ሁሉ አማን ሁሉ ሰላም ነው? የኔ ነገር መቼም ሰሞኑን ሳቀርባቸው የነበሩ አጫጭር ጨዋታዎች ላይ አንድም ግዜ እንኳ ሰላም ሳልልዎት ቀጥታ ወደ ወሬዬ ስገባ “እንዴት ያለው ወሬኛ ወጥቶታል!?” ብለው ሳይታዘቡኝ አይቀሩም። ለዚህ ነው ዛሬም ሌላ ትዝብት ሳይከተለኝ ቀድሜ ሰላምታ ያቀረብኩት። “ምናለ ሁሉ ሰው እንዳተ ከጥፋቱ ቢፀፀት” ይበሉና ያኩሩኝ እንጂ…

እኔ የምልዎ ወዳጄ እኒህ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ከዚህ በፊት ባንዲራን “ጨርቅ” ብለውት አስኮርፈውን አልነበር? ከዛ በስንት ግዜው “የባንዲራ ቀን” ብለው አሳውጀው ክብረ በዓል ክብረ በዓል ሲያንበሻብሹን ህዝቡ “በአስራ ምናምን አመታቸውም ቢሆን እንኳን ተፀፀቱ” ብሎ ይቅር ብሏቸው ሲያበቃ፤ አሁን ደግሞ ሰው አያየኝም ብለው ነው መሰል፣ በጎረቤት አገር ኬኒያ ባንዲራውን እንዴት እንዴት እንደዘቀዘቁት ተመለከቱልኝ?

አይዬ… እኚህ ሰውዬ ምን እየነካቸው እንደሆን እንጃ? ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነውብኝ እንጂ (አድሮ ቃሪያ ሆኑሳ! ብዬ ብተርትባቸው ደስታዬ ነበር።)

የምር ግን ጠቅላይ ሚኒስትራችን ምን እየነካቸው ነው እንዲህ ህዝባቸው እንደ አይኑ የሚያየውን ነገር ሁላ ማጣጣል እና ማንቋሸሽ የሚቀናቸው። አንዳንድ በነገሩ ብስጭት ያሉ ግለሰቦች ምን እያሉ እንደሚናገሩ ሰምተውልኛል? “አቶ መለስ ልክ እኛን በጠቅላይ ሚኒስትርነት መጠቅለል የጀመሩ ግዜ እርኩስ መንፈስ ደግሞ እርሳቸውን ጠቅሏሏቸዋል!” እያሉ እየተናገሩቸው እኮ ነው።
ባንዲራ የሀገራችን ሰው በጣም የሚያከብረው ትልቅ ዋጋ የሚሰጠው ነገር ነው። (እኔ ራሴ አሁን “ነገር ነው” ስላልኩ ህዝቤን ይቅርታ ጠይቃለሁ።) የኛ ሰው ሲለምን እንኳ “አረ በባንዲራው…” ብሎ ከጠየቀ “የለኝም” አይባልም። በአዲሱ የባንዲራ አዋጅ ሳይከለከል አይቀርም እንጂ፤ ህዝቡ ባንዲራውን ከመውደዱ የተነሳ በሰርጉ፣ በለቅሶው፣ በቤት ምርቃቱ ሁሉ አይለየውም።

በነገራችን ላይ አዲሱን የባንዲራ አዋጅ ጠንቅቀው ያውቁታል? (ይሄኔ በሆድዎ… በየቀኑ አዳዲስ አዋጅ ይወጣልና ስንቱን አውቀዋለሁ? ብለው ሊጠይቁኝ እንደሚችሉ እጠረጥራለሁ።) የምርም ግን አገራችን በኢኮኖሚ እድገት ብቻ ሳይሆን በአዋአጅ እድገትም ከሌሎች አገራት ጋር ስትነፃፀር ታላቅ እመርታ እያሳየች እኮ ነው። የመያድ አዋጅ፣ የሽበርተኞች አዋጅ፣ የመሬት አዋጅ የባንዲራ አዋጅ… የወዘተ አዋጅ… (ይህንን ልብ ያለ አንድ ወዳጄ ምን አለ መሰልዎ…? ይቺ ሀገር ከዚህ በፊት በምን ነበር የምትተዳደረው…? ብሎ ጠይቆናል። አንድ ችኩል መላሽ ታድያ “በግብርና” ብሎ መልሶለታል።
በሰንደቅ አላማው አዋጅ በርካታ ነገሮች ተካተዋል። አብዛኛዎቹ በኮከቧ ለይ ያጠነጠኑ ሲሆኑ፤ በጥቅሉ ግን “ባንዲራን ያዋረደ ይዋረዳል” አይነት ትርጉም አለው።

እና ታድያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አዲሱ አዋጅም ህዝቡም እንዲህ የሚያከብረውን ሰንደቅ እየደጋገሙ ክብሩን ዝቅ ማድረግ ምን ይሉት ፈሊጥ ነው…? ደሞስ ሰሊጥ እንጂ ፈሊት ኤክስፖርት አይደረግ፣ አይለጠለጥ፣ አየሸጥ፣ አይለወጥ…! እውነቴን እኮ ነው በአጉል ፈሊጥ ከህዝብ ጋር ከመቀያየም አራዳ መሆኑ አይሻልም ይላሉ ወዳጄ? ለነገሩ እርድናውስ ከየት ይመጣል? ነገር ግን ቢያንስ ምክር በመስማት አራዳ መሆን ይቻላል።

አረ ጎበዝ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩን መክሮ አራዳ የሚያደርጋቸው፤ አንድ ሰው እንዴት ይጠፋል? አስቲ በቅርብ የምታገኟቸው ከሰሙ በምክር ካልሰሙ በአሽሙር ንገሯቸው፤ ለነፍስ ይሆናችኋል።

እውነቴን እኮ ነው፤ መቼም ጆሮ ለባቤቱ ባዳ ነው። የሳቸውንም ጆሮ ደፍረን ባዳ ነው ባንለው እንኳ ቢያንስ ግን “ያኮረፈ ዘመድ” ከመሆን አያመልጥም እና፤ ስለርሳቸው የሚባለውን በሙሉ አጥርቶ የሚሰማላቸው አልመሰለኝም።

ቢሰሙማ ኖሮ ቢያንስ ትንሽ ትንሽ ጥንቃቄ ያደርጉ ነበር። ይህው ባለፈው ሰሞን አያታቸው፤ የአቶ ዜናዊ አባት የሆኑት አቶ አስረስ ለጣልያን በባንዳነት አገልግለዋል። የሚል በፎቶ የተደገፈ መረጃ በፌስ ቡክ ላይ ተለጥፎ ነበር። ይህንን ተከትሎም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ ያሳዩዋቸው ያልተገቡ ባህሪያት ከዛ የተነሳ ነው ብለው የሚጠረጥሩ በርካቶች አስተያየት ሰጪዎች መጥተዋል።

ለምሳሌ ከኤርትራ ጋር ያንን ሁሉ ጦርነት አድርገን ስናበቃ ራሳችን ባሸነፍነው ጦርነት ባድመ ስትሰጥ ዝም ማለታቸው፣ ከዛ በፊትም ቢሆን አሰብን ያህል ወደብ ለመከራከር የሚያስችላቸው በርካታ ታሪካዊ ማስረጃዎች እየነበሩዋቸው “ግመል ውሃ አጠጡበት” ብለው እንደዋዛ መተዋቸው፣ “የአክሱም ሀውልት ለደቡብ ምኑ ነው?” ብለው ህዝብ እና ህዝብን ማራራቃቸው፣ ባንዲራን ጨርቅ ነው ማለታቸው፣ አሁን ደግሞ ይለይላችሁ ብለው፤ ባንዲራውን መዘቅዘቃቸው… ይሄንን ሁሉ ከአያታቸው አቶ አሰረስ ጋር እያያዙት አሁንም ሰውዬው ሀገሪቷን ጥምድ አድርገገው ከያዙ ጥቅመኛ ባንዳዎች ጋር እያመሳሰሏቸው ነው። ቀድሞ ያደረጉትን እንኳ ይሁን ጉርምስናም ጉልምስናም ይዟቸው ነበር ብለን እናስብ…!

ይሄ የሆነው ግን አሁን በቅርቡ ነው። ኬኒያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ እና የኛ
ይቱ ኢትዮጵያ ላሙ የተባለ የጋራ ወደብ ለመገንባት ኬኒያ ላይ ተገናኝተው ነበር። እንግዲህ በዚህ ዝግጅት ላይ ነበር ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ክቡሩን ባንዲራ (ለዛውም ኮከብ ያለበትን… ምን ያስቅዎታል?) እውነቴን ነውኮ አዲሱ የባንዲራ አዋጅ “ኮከብ የሌለው ባንዲራ መያዝ ነውር ነው” ብሎናል…! በርግጥ በዛው ልክ ባንዲራውን መዘቅዘቅም ነውር ነው። እርሳቸው ግን ዘቅዝቀው ይዘውታል።

እስከ ዛሬ ድረስ እንደምናውቀው ባንዲራ የሚዘቀዘቀው ወይም የሚቃጠለውና የሚቀደደው በሀገሩ መንግስት ላይ ተቃውሞን ለመግፅ ነበር። ታድያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህዝቡን ነው የራሳቸውን መንግስት ነው የሚቃወሙት…!?
ልቦና ይስጣቸው ወይም ሌላ የሚወዱት ሀገር እና የሚወዱት ባንዲራ ይስጣቸው ብዬ በአንድ እግሬ ቆሜ እፀልያለሁ! ያግዙኝ ወዳጄ!
በመጨረሻም
“ይሄን ጉድ አየህው?” ብሎ ፎቶግራፉን የላከልኝን የልብ ወዳጄ ሲሳይን አመስግኑልኝ።
ትዝታ ዘ ባንዲራ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዘቀዘቁት ባንዲራ
ትላንት በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ላይ ኢቲቪ አንድ ግለሰብ የሆነ ነገር ሲያውለበልብ አሳየንናተቃዋሚዎቹ  ለባንዲራ የሚሰጠውን ክብር በማንቋሸሽ የተቀዳደደ ባንዲራ ሲያውለበልቡ ነበር ብሎ አሳየን… 1ኛ … ያ ሰውዬ የተቃዋሚዎቹ ተወካይ ስለመሆኑ ምንም ማስረጃ የለም፡፡ 2ኛ የያዘው ነገር ባንዲራ ስለመሆኑም መለየት አልተቻለኝም… የሆነ ሆኖ… ይቺ ዜና ወሬ ከየት ትዝ እንዳለችኝ እንጃላቷ…  ድጋሚ አትሜያታለሁ….

ጤና ይስጥልጅ ወዳጄ እንዴት አሉልኝ። ጤና ኑሮ ሁሉ አማን ሁሉ ሰላም ነው? የኔ ነገር መቼም ሰሞኑን ሳቀርባቸው የነበሩ አጫጭር ጨዋታዎች ላይ አንድም ግዜ እንኳ ሰላም ሳልልዎት ቀጥታ ወደ ወሬዬ ስገባ “እንዴት ያለው ወሬኛ ወጥቶታል!?” ብለው ሳይታዘቡኝ አይቀሩም። ለዚህ ነው ዛሬም ሌላ ትዝብት ሳይከተለኝ ቀድሜ ሰላምታ ያቀረብኩት። “ምናለ ሁሉ ሰው እንዳተ ከጥፋቱ ቢፀፀት” ይበሉና ያኩሩኝ እንጂ…

እኔ የምልዎ ወዳጄ እኒህ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ከዚህ በፊት ባንዲራን “ጨርቅ” ብለውት አስኮርፈውን አልነበር? ከዛ በስንት ግዜው “የባንዲራ ቀን” ብለው አሳውጀው ክብረ በዓል ክብረ በዓል ሲያንበሻብሹን ህዝቡ “በአስራ ምናምን አመታቸውም ቢሆን እንኳን ተፀፀቱ” ብሎ ይቅር ብሏቸው ሲያበቃ፤ አሁን ደግሞ ሰው አያየኝም ብለው ነው መሰል፣ በጎረቤት አገር ኬኒያ ባንዲራውን እንዴት እንዴት እንደዘቀዘቁት ተመለከቱልኝ?

አይዬ… እኚህ ሰውዬ ምን እየነካቸው እንደሆን እንጃ? ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነውብኝ እንጂ (አድሮ ቃሪያ ሆኑሳ! ብዬ ብተርትባቸው ደስታዬ ነበር።)

የምር ግን ጠቅላይ ሚኒስትራችን ምን እየነካቸው ነው እንዲህ ህዝባቸው እንደ አይኑ የሚያየውን ነገር ሁላ ማጣጣል እና ማንቋሸሽ የሚቀናቸው። አንዳንድ በነገሩ ብስጭት ያሉ ግለሰቦች ምን እያሉ እንደሚናገሩ ሰምተውልኛል? “አቶ መለስ ልክ እኛን በጠቅላይ ሚኒስትርነት መጠቅለል የጀመሩ ግዜ እርኩስ መንፈስ ደግሞ እርሳቸውን ጠቅሏሏቸዋል!” እያሉ እየተናገሩቸው እኮ ነው።

ባንዲራ የሀገራችን ሰው በጣም የሚያከብረው ትልቅ ዋጋ የሚሰጠው ነገር ነው። (እኔ ራሴ አሁን “ነገር ነው” ስላልኩ ህዝቤን ይቅርታ ጠይቃለሁ።) የኛ ሰው ሲለምን እንኳ “አረ በባንዲራው…” ብሎ ከጠየቀ “የለኝም” አይባልም። በአዲሱ የባንዲራ አዋጅ ሳይከለከል አይቀርም እንጂ፤ ህዝቡ ባንዲራውን ከመውደዱ የተነሳ በሰርጉ፣ በለቅሶው፣ በቤት ምርቃቱ ሁሉ አይለየውም።

በነገራችን ላይ አዲሱን የባንዲራ አዋጅ ጠንቅቀው ያውቁታል? (ይሄኔ በሆድዎ… በየቀኑ አዳዲስ አዋጅ ይወጣልና ስንቱን አውቀዋለሁ? ብለው ሊጠይቁኝ እንደሚችሉ እጠረጥራለሁ።) የምርም ግን አገራችን በኢኮኖሚ እድገት ብቻ ሳይሆን በአዋአጅ እድገትም ከሌሎች አገራት ጋር ስትነፃፀር ታላቅ እመርታ እያሳየች እኮ ነው። የመያድ አዋጅ፣ የሽበርተኞች አዋጅ፣ የመሬት አዋጅ የባንዲራ አዋጅ… የወዘተ አዋጅ… (ይህንን ልብ ያለ አንድ ወዳጄ ምን አለ መሰልዎ…? ይቺ ሀገር ከዚህ በፊት በምን ነበር የምትተዳደረው…? ብሎ ጠይቆናል። አንድ ችኩል መላሽ ታድያ “በግብርና” ብሎ መልሶለታል።

በሰንደቅ አላማው አዋጅ በርካታ ነገሮች ተካተዋል። አብዛኛዎቹ በኮከቧ ለይ ያጠነጠኑ ሲሆኑ፤ በጥቅሉ ግን “ባንዲራን ያዋረደ ይዋረዳል” አይነት ትርጉም አለው።

እና ታድያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አዲሱ አዋጅም ህዝቡም እንዲህ የሚያከብረውን ሰንደቅ እየደጋገሙ ክብሩን ዝቅ ማድረግ ምን ይሉት ፈሊጥ ነው…? ደሞስ ሰሊጥ እንጂ ፈሊት ኤክስፖርት አይደረግ፣ አይለጠለጥ፣ አየሸጥ፣ አይለወጥ…! እውነቴን እኮ ነው በአጉል ፈሊጥ ከህዝብ ጋር ከመቀያየም አራዳ መሆኑ አይሻልም ይላሉ ወዳጄ? ለነገሩ እርድናውስ ከየት ይመጣል? ነገር ግን ቢያንስ ምክር በመስማት አራዳ መሆን ይቻላል።

አረ ጎበዝ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩን መክሮ አራዳ የሚያደርጋቸው፤ አንድ ሰው እንዴት ይጠፋል? አስቲ በቅርብ የምታገኟቸው ከሰሙ በምክር ካልሰሙ በአሽሙር ንገሯቸው፤ ለነፍስ ይሆናችኋል።

እውነቴን እኮ ነው፤ መቼም ጆሮ ለባቤቱ ባዳ ነው። የሳቸውንም ጆሮ ደፍረን ባዳ ነው ባንለው እንኳ ቢያንስ ግን “ያኮረፈ ዘመድ” ከመሆን አያመልጥም እና፤ ስለርሳቸው የሚባለውን በሙሉ አጥርቶ የሚሰማላቸው አልመሰለኝም።

ቢሰሙማ ኖሮ ቢያንስ ትንሽ ትንሽ ጥንቃቄ ያደርጉ ነበር። ይህው ባለፈው ሰሞን አያታቸው፤ የአቶ ዜናዊ አባት የሆኑት አቶ አስረስ ለጣልያን በባንዳነት አገልግለዋል። የሚል በፎቶ የተደገፈ መረጃ በፌስ ቡክ ላይ ተለጥፎ ነበር። ይህንን ተከትሎም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ ያሳዩዋቸው ያልተገቡ ባህሪያት ከዛ የተነሳ ነው ብለው የሚጠረጥሩ በርካቶች አስተያየት ሰጪዎች መጥተዋል።

ለምሳሌ ከኤርትራ ጋር ያንን ሁሉ ጦርነት አድርገን ስናበቃ ራሳችን ባሸነፍነው ጦርነት ባድመ ስትሰጥ ዝም ማለታቸው፣ ከዛ በፊትም ቢሆን አሰብን ያህል ወደብ ለመከራከር የሚያስችላቸው በርካታ ታሪካዊ ማስረጃዎች እየነበሩዋቸው “ግመል ውሃ አጠጡበት” ብለው እንደዋዛ መተዋቸው፣ “የአክሱም ሀውልት ለደቡብ ምኑ ነው?” ብለው ህዝብ እና ህዝብን ማራራቃቸው፣ ባንዲራን ጨርቅ ነው ማለታቸው፣ አሁን ደግሞ ይለይላችሁ ብለው፤ ባንዲራውን መዘቅዘቃቸው… ይሄንን ሁሉ ከአያታቸው አቶ አሰረስ ጋር እያያዙት አሁንም ሰውዬው ሀገሪቷን ጥምድ አድርገገው ከያዙ ጥቅመኛ ባንዳዎች ጋር እያመሳሰሏቸው ነው። ቀድሞ ያደረጉትን እንኳ ይሁን ጉርምስናም ጉልምስናም ይዟቸው ነበር ብለን እናስብ…!

ይሄ የሆነው ግን አሁን በቅርቡ ነው። ኬኒያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ እና የኛይቱ ኢትዮጵያ ላሙ የተባለ የጋራ ወደብ ለመገንባት ኬኒያ ላይ ተገናኝተው ነበር። እንግዲህ በዚህ ዝግጅት ላይ ነበር ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ክቡሩን ባንዲራ (ለዛውም ኮከብ ያለበትን… ምን ያስቅዎታል?) እውነቴን ነውኮ አዲሱ የባንዲራ አዋጅ “ኮከብ የሌለው ባንዲራ መያዝ ነውር ነው” ብሎናል…! በርግጥ በዛው ልክ ባንዲራውን መዘቅዘቅም ነውር ነው። እርሳቸው ግን ዘቅዝቀው ይዘውታል።

እስከ ዛሬ ድረስ እንደምናውቀው ባንዲራ የሚዘቀዘቀው ወይም የሚቃጠለውና የሚቀደደው በሀገሩ መንግስት ላይ ተቃውሞን ለመግፅ ነበር። ታድያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህዝቡን ነው የራሳቸውን መንግስት ነው የሚቃወሙት…!?

ልቦና ይስጣቸው ወይም ሌላ የሚወዱት ሀገር እና የሚወዱት ባንዲራ ይስጣቸው ብዬ በአንድ እግሬ ቆሜ እፀልያለሁ! ያግዙኝ ወዳጄ!

በመጨረሻም

“ይሄን ጉድ አየህው?” ብሎ ፎቶግራፉን የላከልኝን የልብ ወዳጄ ሲሳይን አመስግኑልኝ።

አቤ ቶኪቻው http://www.abetokichaw.com/

No comments: