Sunday, July 21, 2013

በአዲስ አበባ ከተማ እንጻ ተደርምሶ በ ዘጠኝ ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ተገለጸ :: የሞተመ አለ !

በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶው ጎጃም በረንዳ በተሰኘው አካባቢ ለባቡር ሃዲድ መስሪያ በሚል ሰበብ የመንገድ ቅየሳ በማድረግ ላይ በሚገኘው የግንባታ ስራ ላይ በአካባቢው በሚገኙት ቤቶች ላይ ይፍረስ ላይ የሚል ትእዛዝ የተላለፈባቸው ቤቶች በሙሉ እንፈርሱ እየተደረገ መሆኑን የአዲስ አበባ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት አሳውቆአል ሆኖም በዚህ ሳምንት ውስጥ ከፈረሱት ቤቶች መካከል አንዱ በዜጎች ላይ ክፉኛ አደጋ አድርሶአል ።

በቸልተኝነት ስራ በኑር ህንጻ ላይ የደረሰውን አደጋ ዝም ተብሎ ሲታለፍ በዛሬው እለት ደግሞ የአሰፋ ገለታ ሆቴል እንዲፈር ተደርጎ ሁለት ዎንዶች በመንገድ ላይ ሻይ የምትሸጥ ሴት ህይወታቸው ሲያልፍ እንዲሁም አራት ደላላ ሰዎች ክፉኛ አደጋ ሲደርባቸው ሻይ የሚጠጣ ሰው እና ሌሎችም ከአፍራሽ ቡድኑ ሃይልም በከፍተኛ አደጋ ላይ መውደቃቸውን እና ማንም ሰው ለዚህ ሃላፊነት ሊወስድ የቻለ አካል እንደሌለ ተገልጾአል ።

  መንግስት ለዚህ ሃላፊነቱን ሊወስድ ይገባዋል ሲሉ የአካባቢው ህብረተሰብ ገልጸዋል ።እንደዚህ አይነት አሰቃቂ ጉዳት እንዲደርስ ያደረገው መንግስት መንግስት ለግባታው ሲል ባቀደው ፕሮግራም ስለሆነ አሰቃቂ የሆኑ እና ያልታሰቡ አደጋዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ መገለጽ ሲገባው ምንም ነገር ሳይባል እና ለደህንነት ሲባል የተደረገ ጥንቃቄ ባለመኖሩ ለሚፈርሱት ቤቶች የቤታቸውን ድርሻ እና የህይወት ዋስት ወይንም ኢንሹራንስ መንግስት ሳይወድ በግዱ መስጠት ይገባዋል ሲሉም የህግ ባለሙያዎች አክለው ገልጸዋል ።

ምንጭ maleda times

No comments: