![](https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEiuMDiyjlmAI0Q3kcUNoYuuV8mYi3v7eSG-Dtki3scC2CFfO6i24r7KZPI0bTE7MZfLrvEzZZnv8CsFQRC9ruKc8cdGxaBsQxEg8Kz30hl8IIBaAqkI2pu3mq1vxaKx_InPUuT1M_9BqVE/s1600/Addis-ababa-ethiopia%5B1%5D.jpg)
በቸልተኝነት ስራ በኑር ህንጻ ላይ የደረሰውን አደጋ ዝም ተብሎ ሲታለፍ በዛሬው እለት ደግሞ የአሰፋ ገለታ ሆቴል እንዲፈር ተደርጎ ሁለት ዎንዶች በመንገድ ላይ ሻይ የምትሸጥ ሴት ህይወታቸው ሲያልፍ እንዲሁም አራት ደላላ ሰዎች ክፉኛ አደጋ ሲደርባቸው ሻይ የሚጠጣ ሰው እና ሌሎችም ከአፍራሽ ቡድኑ ሃይልም በከፍተኛ አደጋ ላይ መውደቃቸውን እና ማንም ሰው ለዚህ ሃላፊነት ሊወስድ የቻለ አካል እንደሌለ ተገልጾአል ።
መንግስት ለዚህ ሃላፊነቱን ሊወስድ ይገባዋል ሲሉ የአካባቢው ህብረተሰብ ገልጸዋል ።እንደዚህ አይነት አሰቃቂ ጉዳት እንዲደርስ ያደረገው መንግስት መንግስት ለግባታው ሲል ባቀደው ፕሮግራም ስለሆነ አሰቃቂ የሆኑ እና ያልታሰቡ አደጋዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ መገለጽ ሲገባው ምንም ነገር ሳይባል እና ለደህንነት ሲባል የተደረገ ጥንቃቄ ባለመኖሩ ለሚፈርሱት ቤቶች የቤታቸውን ድርሻ እና የህይወት ዋስት ወይንም ኢንሹራንስ መንግስት ሳይወድ በግዱ መስጠት ይገባዋል ሲሉም የህግ ባለሙያዎች አክለው ገልጸዋል ።
ምንጭ maleda times
No comments:
Post a Comment