Tuesday, September 9, 2014

በብሶት የታፈነው ህዝብ አመፅ ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት ወያኔ አድሮበታል።

Sep 9,2014
 2007 ለለውጥ !
በሳሞራ የኑስ እና በጌታቸው አሰፋ የሚመራ ልዩ የኮማንዶ እና የደህንነት ሃይል አዲስ አበባ ባህር ዳር እና ድሬዳዋን መቆጣጠር የሚችልበትን ስልት እየነደፈ ነው።
- በሳሞራ የኑስ የሚመራው የኮማንዶ ጦር ህገመንግስታዊ ጥያቄ ማንሳቱ ታማኝነቱ ጥርጣሪ ውስጥ ገብቷል
- መጪው ጊዜ በመላው ኢትዮጵያ የአንድነት እና የዲሞክራሲ ሃይሎች ገነው ይወጣሉ።
- ዲያስፖራው ከምንም ጊዜ በበለጠ ለወያኔ የጎን ውጋትና ራስ ምታት ሆኗል።
- ተቃዋሚ ሃይሎች በአሁን ወቅት ከባድ ጥንካሬ እና የትግል ስልት ሊኖራቸው ይገባል።ጊዜው ነው።
ምንሊክ ሳልሳዊ ፦ በብሶት የታፈነው ኢትዮጵያዊ በቀጣዮቹ ጊዜያት ከፍተኛ አመጽ ያስነሳል በሚል ስጋት ያደረበት እና አመፁ ከመንግስት ሃይሎች ቁጥትር ውጪ ይሆናል በሚል ከፍተኛ ውጥረት በስጋት የተደባለቀበት የወያኒው ጁንታ በከፍተኛ ባለስልጣናት ደረጃ ስብስባ የተቀመጠ ሲሆን ካለፉት ሳምንታት ተከታታይ ስብሰባዎች በተገኙ የውይይት ፍሬ ሃሳቦች መሰረት በሳሞራ የኑስ እና በጌታቸው አሰፋ የሚመራ ልዩ የኮማንዶ እና የደህንነት ሃይል አዲስ አበባ ባህር ዳር እና ድሬዳዋን መቆጣጠር የሚችልበትን ስልት እየነደፈ ነው።
በአዲስ አበባ የከፍተኛ ለሕወሓት ባለስልጣናት ቅርብ የሆኑት ምንጮች እንደተናገሩት የሚነደፈው ስልት የሕወሓት ባለስልጣናት እምነት ያልጣሉባቸውን የፖሊስ እና ወታደራዊ ሃይሎችን ጨምሮ ህዝቡን መቆጣጠር በሚቻልበት ሁኒታ ልላ ያተኮረ ሲሆን የፖሊስ እና ወታደሩ ክፍል በባለስልጣናት ላይ እርምጃ ይወስዳል በሚል ከፍተኛ ስጋትም እንዳደረባቸው ታውቋል ። የትግራይ ተወላጆች የሆኑትም ፊታቸውን እንዳዞሩባቸው የጠቆሙት ምንጮቹ በከፍተኛ ገንዘብ ከደቡብ ሱዳን ምስራቃዊ ክፍል የሚገኙ እና በስደተኝነት በኢትዮጵያ የኖሩ አማርኛ ቋንቋን የሚናገሩና የሚሞክሩ እንዲሁም ከኑባ ደማዚን ቅጥረኞችን በመግዛት ከቢንሻንጉል ጉምዝ በማምጣት እንዲሁም አስፈላጊ የሆኑ የቀድሞ ታጋዮችን በፖሊስ መልክ በመመልመል በጥሩ ክፍያ በአዲስ አበባ ባህር ዳር እና ድሬዳዋ ላይ ለማስፈር መታቀዱን ተጠቁሟል። በተለይ በአዲስ አበባ እና በባህር ዳር ይመደባሉ የተባሉ እናበተለያየ ጊዜ በሳሞራ የኑስ የተመረቁ እና በስሩ የሚታዘዙ ኮማንዶዎች እንዲዘጋጁ የተነገራቸው ቢሆንም ባለፈው ሳምንት በነበርቸው ስብሰባ ላይ ህገመንግስታዊ ጥያቂዎችን እንዳነሱ ከታወቀ በኋላ ታማኝነቱ ጥርጣሬ ውስጥ በመግባቱ የወያኒ ስጋቶች ሰፍተው እና ተወጥረው መታየታቸውን ምንጮቹ ተናግረዋል።
የሕዝብ አመጽ ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ይሆናል የሚሉት ባለስልጣናት ወታደሩ ክፍል እና የፖሊስ ሰርዊቱ ስለ ተቃዋሚዎች በጎ አመለካከት እንዳይኖረው ከፍተኛ ፕሮፓጋንዳ በየ ክፍሉ እየረጩ ሲሆን የፖለኢስ እና የጦር ሰራዊቱ ግን ጥያቂዎችን ከማንሳቱም በላይ ከካድሬዎች ጋር ፊት ለፊት እስከመሟገት መድረሱ ከቀረበልቸው ሪፖርት የተረዱት ወያኔዎች እንዲሁን ይህን ሰሞን በተለያየ መልኩ አብዮታዊ ዲሞክራሲ በልማት ስም ሽፋን በማድረግ በስልተና መልክ ሲሰጡ የገጠማችው ተቃውሞ ካድሬዎች ፖሊሰና ሰርዊቱ ሕገመንግስታዊ ጥያቄ እንዲያነሳ ማድረጉን የሚያስገነዝብ ሪፖርት በስፋት እንደቀረበ እና ይህንን ሪፖርት ተገትሎ የህዝብ ብሶት ይፈነዳል የሚል ስጋት ወያኒን እያሯሯጠው እንደሆነ ታውቋል።
ምንጮቹ አያይዘውም መጪው ጊዜ በመላው ኢትዮጵያ የአንድነት እና የዲሞክራሲ ሃይሎች ገነው ይወጣሉ። የሚልው የወያኒ ዋና የስብሰባ ነጥብ ገነው እንዳይወጡ በተለይይ የማምከን ስራ ለመጠቀም ቢያስብም ካሁን በፊት የተጠቀመብት ስልት እንዳላዋጣው እና ተቃዋሚዎች ገነው እንዳይወጡ የሚያደርግ የመጨረሻ እርምጃ ለመውስድ የሚያስችል ጥናት በአቶ በርክት ስምኦን በኩል በአስቸኳያ እንዲጠና ሲል ዲያስፖራው ከምንም ጊዜ በበለጠ ለወያኔ የጎን ውጋትና ራስ ምታት እንደሆነና የሀገር ውስጥ ተቃዋሚዎችን በማደረጀት ረገድ ትልቁን ሚና እየትጫወተ እንደሆነ መወሳቱን እና ይህንን ወያኔ መቆጣጠር እንዳቃተው እንደቀጠለ እንዳለ ተነግሯል። ምንጮቹ አያይዘውም ተቃዋሚ ሃይሎች በአሁን ወቅት ከባድ ጥንካሬ እና የትግል ስልት ሊኖራቸው ይገባል ፤ጊዜው ነው። ሲሉ መረጃውን አድርሰውናል።
በሃገር ውስጥ እና በውጪው ህገር የምንገኝ ተቃዋሚዎች ወያኒ በገባበት ስጋት እና ውጥረት ውስጥ ራሱን በራሱ እንዲቀብር ና በኢትዮጵያ ለአንዲና ለመጨረሻ ጊዜ አምባገነንነት እንዲያከትም የዜግነት ድርሻችንን በጋራ የምንወጣብት ጊዜ አሁን በመሆኑ በጋራ ልዩነቶችን በማቻቻል አንዱ አንዱን ሳይወንጅል እና ሳይፈርጅ በተባበረ ክንድ በተገኘው የትግል ስልት ልይ ሁሉ በተገኘው ድርጅት ጋር ሁሉ በመሳተፍ ለነጻነትችን የምንችለውን አስታውጾ ሁሉ እንድናደርግ ይጠበቅብናል። ነጻነት በእጃችን ነው !!

No comments: