Tuesday, September 2, 2014

አቻምና ኢትርሃሞይ ዘንድሮ ጎንታናሞ ቤይ! – ታደለ መኩሪያ

Sep2,2014
Andargachew Tsige
በ1997 ዓ ም  የቅንጅት በምርጫ  ማሸነፍ ያሰጋቸው የወያኔ መሪዎች  በሕዝብ ውስጥ መጠራጠርንና  መከፋፈልን ለመፍጠር ፤ በ1994 ዓ ም በሩዋንዳ የተፈጠረውን የዘር ማጥፋት ተመስሌት  ‘ኢትርሃሞይን’ ተቃዋሚዎች ሊፈጥሩ ነው ብለው ፕሮበጋንዳ ነዙ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለማያውቃችሁ ታጠኑ አላቸቸወ፤ በ1967 ዓ ም  አማርኛ ተናገሪውን ለይተው ለማጥፋት በፕሮገራማቸው ነድፈው መቀሳቀሳቸውን  በእነርሱ ቤት የኢትዮጵያ ሕዝብ አላየም፣ አልሰማም፣ አላነበበም፤ ኩኩ መለኮቴ መሰል  የልጆች ጫወታችሁን ተውና ማለቱን ገና አልገባቸውም፤ በሐምሌ መጨረሻ 2014 ዓ ም    የውጪ ጉዳይ ሚንስትሩ ዶክተር ቴዎድሮስ አድኖምም  በአሜሪካ  በዲሲ  ከተማ ቆይታቸው ባአካባቢው በሚገኝ  ለግል ሬዲዮ ጣቢያ  ቃል መጠየቅ  ሰጥተው ነበር፤ከሁለት ዓመታት  በላይ  በግፍ ታስረው  ሰለሚማቅቁት የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች መፍትሔ አፈላላጊ ተመራጮች  ኮሚቴ ጉዳይ  መጥይቅ ቀርቦላቸው ነበር። የኢትዮጵያ እስልምና ተከታዮችን  በጎንታናሞቤይ ኩባ ሰላጤ፣ በአሜሪካ ባሕር ሃይል መናሕሪያ በአልካይዳነት ተጠርጣረው ከታሰሩት ጋር  አመሳስላዋቸዋል። በጣም የሚያስደነግጥና የሚያስፈራ ፍረጃ፣ ኢትዮጵያ በሃይማኖት መቻቻል በዓለም ሕብረተሰብ የምትጠቀሰውን ሀገር በአንድ ጎርዳፋ ምላስ አፈር አበሏት፤ ከዚህ በፊትም ዶክተሩ ሰለእነዚሁ ‘ደምፃችን ይሰማ’ በማለት ፍትህን ሰለጠየቁት ሙስሊም ወንዶሞቻች ላይ የተዛባ ዘገባ በማቅረባችው ‘ትልቁ  ዳባ ሊጥ ሆነ’   በሚል መጣጣፍ ምክር መስል ሐሳብ አቅረቤላቸው ነበር። መዋሸትን ማደሪያቸው ካደረጉት ካድሬዎች  ከነሺመልስ ከማልና ከበረከት ሰዕሞን ራሶን ያርቁ የሚል ነበር፤ አልተቀበሉኝም፤ ደግመው ደጋግመው ዋሹ፤ የኢትዮጵያ የእሰልምና ተከታዮችን በአልካይዳነት መፈረጁ ሣህለን ማርያም  የሚያሰኝ ነው፣ ሌላው ደግሞ  በሰኔ ወር 2014 ዓ ም አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ  ከየመን ሳና አይሮፕላን ጣቢያ መታፈን  ሲጠየቁ ይሰጡት የነበረው መልስ የውጭ ጉዳይ ሚንስትርን የሚመጥን መልስ አልነበረም። በሌላ ኃይል ከጀርባ እንደሚነዱ የሚያሳይ ነበር፤ በአቶ አባይ ጸሐዬና በአለቃ ጸጋዬ በረሄ የዘር ተፋሰስ ፓለቲካ እየተገፉ  የማይመጥናቸውን አስነዋሪ  ሥራ  መስራታቸው ለቤተሰባቸው ብቻ ሳይሆን ሞያቸወ ከልብ ለሚወስዱቱ ዜጎች ያሳዝናል፤ ሕብረተሰቡ የሞያቸውን አገልግሎት በጥብቅ ይፈልገዋል። የውጭ ጉዳዩን  ሥራ በአፋቸው ጤፍ ለሚቆሉትና ውሸትን መተዳደሪያቸው ላደረጉት  ለሬደዋን ሁሴን ወይም ለሽፈራው  ሽጉጤ ቢለቁላቸው መልካም ነው። በውሸት መኮራኩር ከሚገጫገጨው ከትግራይ ጉጅሌዎች መንገሥት አባል የነበረው ኤርሚያስ ለገሠ ‘የመለስ  ቱሩፋቶች’ ባለቤት የሌላት ከተማ በሚለው መጸሐፉ ውስጥ ጥሩ ሥዕብና እንዳሎት፣ በ1997 ዓ ም ምርጫን አስመልክቶ ያቀረቡትን ሪፖርት፣ መሠረት አድርጎ ትልቅ ሙገሣን ቸሮታል,፤ ሌላው ዶክተር ተብዬው ደግሞ በዘር ፖለቲካ ናላው የዞረ መሆኑንም ሣይገልጽ አላለፈም።
ዶክተር ቴዎድሮስ አባል የሆኑበት የትግራይ ጎጅሌ ዋና አቀንቃኞቹ፤ሟቹ  መለስ ዜናዊ፣ አባይ ጸሐዬ፣ አርከበ ዐቁባይ፣ መስፍን ሰዩም፣ ሰባት ነጋ፣ አለቃ ጸጋዬ በረሄ ሀገር ለመገነጣጠል ለውጭ አገር ምደኞች ያደሩ  መሆናቸውን እያወቁ የእነርሱ አካል መሆኖ ያሳዝናል፡፡ አባቶ ቴዎድሮስ ብለው ሰም ሲያወጥሎት ለአገሩ አንድነት ሕይወቱን የሰዋን የጅግናውን የሐፄ ቴዎድሮሰን ፈለግ ተከትለው ለአንድነት መስዕዋትነት እንዲከፍሉ ነው።  በዘርና በሃይማኖት ሕዝቡን ከሚያለያዩት ከትግራይ ጉጅሌዎች ጋር ሀገርን በሃይማኖትና በዘር እንዲከፋፍሉ አልነበረም፤  ሰምን መላዓክ ያወጣዋል፣አንድአርጋቸውና ቴዎድሮስ  ለሀገር አንድነት  ተመስሌዎች ናቸው፤ ዶክተር ቴዎድሮስ አድኖምና አንድአርጋቸቸች ጽጌ ወንድማማቾች ናቸው፣ ማን ቃኤል ማን  አቤል እንደሆነ ሥራቸውና ትውልድ ይመስክር፤ ዶክተር ቴዎድሮሰ አድኖም  ወይስ አንድአርጋቸው ጽጌ የአባቶችን  ቃል  ያፈረሰው?  አቶ አድኖም ልጃቸውን ቴዎድሮስ በለው ሰመ ሲያወጡለት ለአንድነት በመሰዕዋትነት ክበርን፣  እንደሚያጎናጽፍ አምነውበት ነው። አቶ ጽጌም ልጃቸውን አንድአርጋቸው ብለው ስም ሲያወጡለት  በአንድነት ጸጋን አብስር ማለታቸው ነው። ኢትዮጵያ  የነዚህ የባለራዕይ  አባቶች ሀገር ናት።  ከትንታኔው ማንኛቸው ናቸው የእሣት ልጅ አመድ የሚባሉት?  ዶክተር ቴዎድሮስ አድኖም ወይስ አንድአርጋቸወ ጽጌ? አደራ ያልበላውን አንድአርጋቸውን አድባር ትከተለው፤  ዶክተር ቴዎድሮስ አድኖምም  በሃይማኖትም በዘር ከፋፋይ ከሆኑት  የትግራይ ጉጅሌዎች  እጅ ወጥተው ከሕዝብ ጎራ ይቀላቀሉ።የአባቶን ሕልም ዕውን ያድርጉ እላለሁ። ኢትዮጵያ  ከወደቀችበት በልጆቿ ትነሣለች።

No comments: