Saturday, September 20, 2014

በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ የጻፈው “የነፃነት ድምጾች፤ ከማዕከላዊ እስከ ዝዋይ ግዞት” መጽሐፍ ወጣ

September 
14 ዓመት ተፈርዶበት እስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ የጻፈው “የነፃነት ድምጾች፤ ከማዕከላዊ እስከ ዝዋይ ግዞት” መጽሐፍ በገበያ ላይ መዋሉን ከአዲስ አበባ ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመከተ።
በዝዋይ ጨለማ እስር ቤት ውስጥ እንደጻፈው በሚነገው በዚህ መጸሐፍ ጋዜጠኛው ክስ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ እስከአሁን ድረስ የገጠመውን ውጣ ውረድ ዘርዝሮ ጽፎታል።
በአራት ም ዕራፎች እንደተከፈለ በተነገለጸለት በዚህ “የነፃነት ድምጾችን ከማዕከላዊ እስከ ዝዋይ ግዞት” መጽሐፉ ስለእስረኞች አያያዝ፣ ከፖሊሶች ጋር ስላለው መስተጋብር፣ ስለሰብአዊ መብት ጥሰት፣ የአገሪቱ ትልልቅ ባለስልጣናት ከነበሩ እስረኞች ጋር ስላደረገው ቃለ ምልልስና ስለታሰረባቸው ወህኒ ቤቶች ገጽታ ያስቃኛል ተብሏል፡፡ መጽሐፉ በኢትዮጵያ በ50 ብር ከ60 ሳንቲም እየተሸጠ ነው።
yenestanet dimstoch

No comments: