Tuesday, September 23, 2014

አሳዛኝ ዜና (ከቂልንጦ እስር ቤት)

September 23,2014
ዛሬ ከወደ ቂልንጦ የደረሰኝ መረጃ እጅግ የሚዘግንና እንቅልፍ የሚነሳ ነው ነገሩ እንዲህ ነው””
አበበ ካሴ ግንቦት ሰባት ነህ ተብሎ የታሰረ ወጣት . በቂልንጦ ይገኛል፡፡ በሚዘገንን መልኩ ቅጣት ብለው የ10 ጣቶቹን ጥፍሮች ነቅለዋቸዋል፡፡ ብልቱ ላይ ሀይላንድ እያንጠለጠሉ ሲያሰቃዩት ቆይተዋል፡፡ ከብልቱ ፈሳሽ መውጣት ጀምሯል ፡፡ እንዲያሳክሙት ቢጠይቅም እምቢ ብለዉ ህክምና ከልክለውታል፡፡ ይባስ ብለው የእስረኛ መለያ መታወቂያውን ቀምተውታል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ይገኛል፡፡ ይህ የጭካኔ ተግባር በምን አይነት ቋንቋ እንደሚገለጽ አላውቅም።

No comments: