Saturday, September 13, 2014

ሰበር ዜና፡ ታጋይ ዘመነ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል አመራር ከአባይ ሚደያ ጋር አጭር ቆይታ አደረገ

September 13, 2014
ሰበር ዜና፡ ታጋይ ዘመነ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል አመራር ከአባይ ሚደያ ጋር አጭር ቆይታ አደረገ።

አባይ ሚዲያ ከግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል የፖለቲካ ሃላፊ ከሆነው ታጋይ ዘመነ ካሴ ጋር የስልክ ውይይት አደረገ። ታጋይ ዘመነ ለአባይ ሚዲያ ሲናገሩ አቶ ኤልያስ ጋዜጠኛ ስለመሆኑም እና እንዴት እና በምን ሂሳብ ወደ ትግል አለም እንደገባም እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ወጣቱ ታጋይ ዘመነ ለኢትዮጵያ ህዝብ ባስተላለፈው መልእክት አዲሱ አመት የሰላም እና የድል ዘመን እንዲሆን በመመኘት እና ወንድማችን ታጋይ አንዳርጋቸውን የከፈለውን መሰዋእትነት ከንቱ እንዳይሆን ህዝባዊ ሃይሉ እና ከሌሎች የነጻነት ሃይሎች ጋር እየተደረገ ያለው ሂደት መፋጠኑን በዚህ አመት የምናወራበት ሳይሆን ወደ ትጋበር ተሸጋግረን ወያኔን የምናበረክክበት ዘመን እንደሚሆን አትጠራጠሩ ሲል መልእክቱን አስተላልፉል።
አባይ ሚዲያ ሰሞኑን ስለ ታጋይ ዘመነ እና ግንቦት 7 በኢትዮጵያን ሪቪው ባለቤት አቶ ኤልያስ ክፍሌ እያደረገ ያለውን ግንቦት 7ን የማጥላላት ዘመቻን አስመልክቶ  ላቀረብንለት ጥያቄ ሲመልስ፡-
በመጀመሪያ እንደዚህ አይነት ለወረደ እና ትግልን ለመጉዳት ሲል ቀን ከሌት በሚሰራ ግለሰብ የሚለውን መመለስ ለእኔ ራሱ ተገቢ አይደለም። እኛ ያለነው ተግባራዊ ትግል ላይ ነው እንጂ ምኞት ላይ አይደለም። እናም እኔ ራሴን ዝቅ አድርጌ በተራ ጉዳዮች መግባት አልፈልግም የኢትዮጵያ ህዝብ ከእኛ ብዙ ይጠብቃል። እውነተኛ ታጋይ፣ እውነተኛ ጋዜጠኛ፣ እውነተኛ ሰራተኛ ሀገራችን ካጣች እኮ ቆዪ፤ ስለዚህ ኤልያስም ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ትግሉን ለመጉዳት ከሚሰሩ ተኩላዎች መጠንቀቅ እና እነሱ የሚመሩትን የግል ዌብሳይት የመረጃ ምንጭ አድርጎ አለመውሰድና አለማየት ተገቢ ነው። ምክንያቱም ለደቂቃም ቢሆን ያዘናጋናል አሁን አንተ ስትደውልም ስራ ትቼ ነው የማናግረው። ብዙ እና በርካታ ስራዎች አሉብን አጣዳፊ የሆኑ።
አባይሚዲያ፡ ሙሉውን ቃለምልልስ ከኢሳት የማክሰኞ ዝግጅት በኋላ ይዞ የሚቀርብ መሆኑን ለአንባቢዎቹ ይገልጻል።
Source: Abbaymedia.com

No comments: