Wednesday, September 24, 2014

ወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ላይ ዋሽተው ስልኩን ጆሮው ላይ ዘጉት

September 24,2014
የኢሳቱ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና መረጃ ፍለጋ ወ/ሮ አዜብ ጋር ደውሎ ድምፃቸውን ኢሳት ራድዮ ላይ አሰምቶናል። ጋዜጠኛ ሲሳይ ወ/ሮ አዜብ መሆናቸውን ካረጋገጡለት በኋላ መረጃ እንዲሰጡት ጠየቃቸው። አድዋ ስለሆንኩ መረጃ የለኝም በሚል ስልኩን ዘጉት። ለሁለተኛ ጊዜ ደወለላቸውና “ዶ/ር ካሱ ኢላላ ከእርስዎ ጋር ባላቸው አለመግባባት ስላላቸው የመለስን ፋውንዴሽን ለቀዋል የሚባል ነገር አለና ይህን እንዲያረጋገጡልኝ ወይም እንዲያስተባብሉልን ነው የደወልኩት” አላቸው። ምንም አይነት ችግር እንደሌለባቸው ከተናገሩ በኋላ መልሰው እርሳቸው ወ/ሮ አዜብ እንዳልሆኑ በድምጽ ተናግረው ዋሹ። “ድምጽዎት እኮ የአዜብ መስፍንን ይመስላል” አላቸው እርሳቸው ግን ልክ ይህን ሲላቸው ለሁለተኛ ጊዜ ስልኩን ዘግተውበታል። የዛሬው ኢሳት ራድዮ ለዚህ ዘገባ ምላሽ አለው ያድምጡት።

No comments: