Thursday, July 10, 2014

እንደ አመራር ከዚህ ስርአት እስር አይደለም ግድያዉንም የምንጠብቀዉ ነዉ፡፡

July 10/2014
ተክሌ በቀለ

ስንቱን ወጣት በቅርቡ ገድሎም የለ፡፡ጠላቶቼ ለሚለዉ ብቻ ሳይሆን ከራሱ የሚቃወሙትንና የሚያምኑቱንም ገዳይ ተፈጥሮ እንዳለዉ እድሜ ለእነ አስገደ ገ/ስላሴ አዉቀናል፡፡በቅርቡም ወጣቱ ዮናስ በላይ ያቅሙን አሳይቶናል( በዚህ አጋጣሚ በረታ ዮኒ)፡፡ለወንዙ ልጆችና ለጓዶቹም እንደማይሆን እናዉቃልን፡፡ዓረና እንደፓርቲ ከተቋቋመ ወዲህ ስንቱ ገበሬ በእስር እየተሰቃየ እንዳለ ፓረቲዉ እንደሌሎቹ እየጮኀ ሲሆን ባለጠመኔዉና እስክረቢቶዉ አብረሃ ደስታ በከፍተኛ አመራር ደረጃ ተጠቂ መሆኑ ነዉ፡፡ሃብታሙ አያሌዉና ዳንኤል ሽበሺ ፍጹም ሰላማዊ ታጋዮች ናቸዉ፤ሌሎችም፡፡እስሩ ቀጥሏል፤ሊቀጥል ይገባል፡፡ይህ ስርአት እስካለ ድረስ ማለቴ ነዉ፡፡ለዉጥ ፈላጊ ከሆነ ለመንም አይቀርለትም፡፡የአንድነትና መኢኣድ(ለግዜዉ ለያይቸ ልጥራቸዉ)፤የመድረክ፤የሰማያዊ፤የትብብርና ሌሎች ፓርቲዎች አመራርና አባላት (እባካችሁ እንወሃድ ወይእንተባበር!) ጠንክረን በመስራት የእስርን ፍርሃት እንደነ አንዷለም፤በቀለ፤ርእዮት፤እስክንድር….እንስበር!! ለመታሰር እንስራ
ልጆቻቸዉና ደጋፊዎቻቸዉ ይፈሩ፤በዉጭም ያላችሁም ኑና በሰላማዊ ትግል እየታሰርን ይህን ስርኣት እንለዉጥ፤እስክንድር እንዳለዉ ይሁን፤እስርበቱን እንሙላዉ፡፡ሃብታሙ አምነሃለሁ፤ህዉሓት/ኢህኣዴግ ይወድቃል! ለዉድቀት ስለሚሰራ!!!

No comments: