Tuesday, July 1, 2014

የአቶ አንዳርጋቸውን ጽጌን በየመን መታፈን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን የተለያዩ አስተያየቶችን እያሰጡ ነው

July 1/2014
ሰኔ ፳፬(ሃያ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የየመን የጸጥታ ሃይሎች የግንቦት7 ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸውን ማፈናቸውን ተከትሎ በፌስቡክ፣ በቲውቲርና በድረገጾች ላይ የተለያዩ አስተያየቶች ተሰጥተዋል።

አክቲቪስት አበበ ገላው በበኩሉ የመን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ማገቷ   ሌላአደገኛና በጣም አሳሳቢ ክስተት ነው።የአንባገነኑየህወሃትስርወመንግስትተቃዋሚዎችንማንምአገርበምንምአይነትሁኔታማፈን፣ማሰርናማንገገላታትአለምአቀፍህግንየሚጥስህገወጥድርጊትነው።የመንአቶአንዳርጋቸውንለወያኔአሳልፋእንዳትሰጥናያለምንምቅድመሁኔታእንድትለቅሁሉምነጻነትናፋቂኢትዮጵያዊሁሉበጋራጥረትሊያደርግይገባል።የየመንኤምባሲዎችንበያሉበትበተቃውሞማጨናነቅናእንቅልፍመንሳትእንዲሁምአለምአቀፍጫናማድረግያስፈልጋል።ግዜሳይረፍድይህንንየቁርጥቀንኢትዮጵያዊለመታደግበያለንበትበጋራእንረባረብ።” ሲል ጥሪ አቅርቧል።

ፕራይድ ዲ ባሰፈረው ጽሁፍ ደግሞ ” እውነተኛ ታጋይ ሊታሰር ሊሞት ይችላል፣ የተጀመረውን ትግል ግን ሊያስሩትም ሆነ ሊገሉት ከቶ አይቻላቸውም። ኢትዮጵያም አንድ አንዳርጋቸውን ብቻ ሳይሆን ሚሊዮን አንዳርጋቸውን ፈጥራለችና በከንቱ አትድከሙ፣ ወደዳችሁም ጠላችሁም ሁላችንም ግንቦት 7 ነን።” ብሎአል።

የአረና ፓርቲ አመራር አባል የሆነው ወጣቱ ፖለቲከኛና መምህር አብራሀ ደስታ ከመቀሌ ባሰፈረው ጽሁፍ ደግሞ ” በርካታኢትዮጵያውያንስደተኞች በየመን ሲሰቃዩ የኢህአዴግ መንግስት ዝምታመምረጡይገርመኝ ነበር።ኢትዮጵያውያን በየመንይታሰራሉ፣ይገረፋሉ፣ይገደላሉ።መንግስትናሀገርየሌላቸውይመስልማንምየሚደርስላቸውየለም።ይህንነገርእንቆቅልሽሆኖብኝነበር።ለካኢትዮጵያውያንስደተኞችበየመንሲሰቃዩየኢትዮጵያመንግስትሰምቶእንዳልሰማየሆነውየየመንመንግስትየግንቦት 7ንአመራርአባላትበመያዝእንዲተባበረውለማግባባትነው።ይሄው ኢህአዴግለዜጎች ደህንነት ሳይሆን ለስልጣኑ የቆመ   የማፍያዎችድርጅትመሆኑአስመሰከረ።መንግስትየሚመሰረተውየህዝብናሀገርደህንነትለመጠበቅነው።ኢህአዴግግንየስደተኞችንደህንነትወደጎንትቶለስልጣኑየሚፈታተኑትንግለሰቦችበመያዝስራተጠምዷል።ለስልጣንጥበቃየሚውልንያህልለዜጎችደህንነትምየሚውልቢኖርመልካምነውእላለሁ።” ብሎአል።

ዘላለም ጸጋየ በበኩሉ ” በሀገራችንመኖርሲያቅተንእንሰደዳለን፡፡
ተሰደንእንኳንእንታደናለን፡፡ኦአምላክሆይምነውእረሳኸን፡፡ኢትዮጵያውያንልጆችህእንደራሄልእንባቸውጸባዖትየሚደርሰውመቸነው፡፡ ጃያስተሰርያ” ያለ ሲሆን፣ ነጻነት ይበልጣል ደግሞ”የመንበኢትዮጵያህዝብየነፃነትትግልላይጣልቃመግባቷንእንድታቆምለጫትናለርካሽለሆነጥቅምየወንበዴስብስብየሆነውወያኔኢህአዴግጋርበማበርታጋዮቿላይእየደረሰላለውአፍናመከራእንግልትተባበሪበመሆንየሀገራችንታሪካዊጠላትእየሆነችእንደምትገኝሊገነዘቡትይገባል:፡” ብሎአል።

የነፃነት ትግል ሁሉንም መራራ መከራ ለመቀበል መፍቀድ ነው በሚል ርእስ ሥርጉተሥላሴ ባወጣችው ጽሁፍ ደግሞ ” የነፃነትትግልመከራንለመቀበልተፈቅዶናተወዶየሚወሰድእርምጃነው።የነፃነትትግልየጫጉላጊዜሽርሽርአይደለም።ሊሆንምከቶውንምአይችልም።ስለዚህ ዛሬ በግንቦት 7ጸሐፊ በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የደረሰው እግታ ከትግልመስምር አንዱ በመሆ ኑ ሊያደናግጥ የሚገባው የዓለም ፍጻሜ አይደለም። ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻችን እራሳቸውን ሰጥተው ነው ኢትዮጵያሀገራችንከክብሯጋርያቆዩን።” ብላለች።

ሙላት ሃይሉ ለየመኑ ፕሬዚዳንት በጻፈው ደብዳቤ ደግሞ ” የየመን መንግስት ከኢትዮጵያ ጋር የሚኖረውን የረጅም ጊዜ የጥቅም ግንኙነት በመመርመር አቶ አንዳርጋቸውን አሳልፎ እንዳይሰጥ ጠይቋል። ሙላት አቶ አንዳርጋቸው በኢትዮጵያ ውስጥ ዲሞክራሲያዊ ስርአት እንዲሰፍን እራሱን አሳልፎ የሰጠ ሰው መሆኑን ገልጿል።

ለኢሳት በኢሜል ከደረሱት መልእከቶች መካከል ፣ አዱኛ የተባሉ ሰው “ለነጻነት በሚደረግ ትግል  ውስጥ መሪ ወይም ታጋይ ቢሞት፣ ቢታሰር ወይም ቢሰደድ ትግል አይቆምም፣ ትግል የሚቆመው ወይም ቅርጹ የሚቀየረው የተፈለገው ነጻነት ሲመጣ ብቻ ነው። አንድ መሪ በመታሰሩ ወይም በመሞቱ ትግል የሚቆም ቢሆን ኖሮ የጆን ጋራንግ ደቡብ ሱዳን ወይም የማንዴላዋ ደቡብ አፍሪካ እስከዛሬም አይወለዱም ነበር። አንዳርጋቸው ጽጌ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ጀግና የነጻነት ታጋዮች መካካል በመጀመሪያው ረድፍ የሚሰለፍ ነው። አንድም ቀን ለልጆቹና ለኑሮው ሳያስብ በረሃ ለበረሃ የሚንከራተት፣ ለአገሩ ነጻነት ሲል ውድ ህይወቱን ለመስጠት ቆርጦ የተነሳ እውነተኛና ጀግና መሪ ነው።  አንዳርጋቸው ቆራጥና ጀግና ሰው ነው። የአገሩ ጉዳይ ሁሌም ስለሚያንገበግበው እረፍት የለውም። የየመን መንግስት አንዳርጋቸውን ለወያኔ ጅቦች አሳልፎ እንደማይሰጠው ተስፋ አደርጋለሁ፣  ቢያደርገው እንኳን ለነጻነት የሚደረገው ትግል መልኩን ቀይሮ፣ እስካሁን ከታየውም በበለጠ ቆራጥነትና አንዳንዴም ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ይካሄዳል እንጅ አይደበዝዝም።  ” ብሎአል።


No comments: