Saturday, July 5, 2014

ኢሳት ከኢትዮጵያ ውስጥ በሚደወሉ የስልክ ደወሎች መጨናነቁን እየገለጸ ነው።

July 4, 2014
ጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም በፌስቡክ ላይ ባስቀመጠው መልክት ላይ በርካታ በሽዎች የሚቆጠሩ ስልኮች የቴሌቪዥን እና ሬዲዮ ጣቢያውን ማጫናነቁን ሲገልጽ ስልክ በመመለስ ተጠምደን ነው የዋልነው በርካታዎቹ ግንቦት 7 አሁኑኑ ለመቀላቀል እና የጀግናውን አንዳርጋቸው ጽጌን ሃሳብና ፍላጎት ለማሳካት መዘጋጀታቸውን እየገለጹ ነው። በሁሉም እድሜ ክልል የሚገኘው ኢትዮጵያዊ ስልክ በመደወል ማዘኑና መቆጨቱን እየገለጸ ሲሆን ሁላችንም አንዳርጋቸው ነን የሚሉ መፈክሮችን ሁሉ እያስቀመጡ ነው።
በተያያዘ ዜና ግንቦት 7 ትግሉ ይፋ መጀመሩን አስታውቋል። ከአዲስ አበባ በደረሰን መረጃ መሰረት ደግሞ የህወሃት/ ወያኔ ባለስልጣናት ከዚህ ጋር በተያያዘ ስብሰባ ላይ መቀመጣቸውን ያረጋገጥን ሲሆን ይህም ከፍተኛ የሆነ የፌድራል ሰራዊቱን የማዘጋጀትና በተጠንቀቅ እንዲሆን ለማዘዝ መሆኑን ዘግቢያችን ጨምሮ ተናግሯል። በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ምንም አይነት ከወትሮው የተለየ እንቅስቃሴ ባይኖርም በአብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ግን በየቤቱ እየተነጋገረ መሆን በተዘዋወረበት መንደሮች ለመረዳት ችሏል። በቦሌ ክፍለ ከተማ መድሃኒያለም አካባቢ ፍሪ አንዳርጋቸው ጽጌ የሚል ጽሁፍ በአውቶብስ መጠበቂያ ተጽፎ መመልከቱንም አክሎ ዘግቦል።
bole_church_ethiopia
ይህ በእንዲህ እንዳለ የወያኔ መንግስት በሀገርና ከሀገር ውስጥ እየተነሳ የመጣውን ቁጣ ሽሽት በሚመስል አንዳርጋቸው ጽጌን አላየሁትም የሚል ወሬ እያስወራ ነው።
ይህ ጠንካራ ታጋይ ወያኔዎቹ ከዚህ በኋላ እያንዳንዷን ጣቶቹ እንኳን እየቆረጡ መግደል ቢጀምሩ አንዳርጋቸው እየሳቀባቸውነው የሚሞተው ያሉት ዶ/ር ብርሃኑ ከዚህ በኋላ ትግሉን ወያኔዎች አስጀምረውታል እየሞትን ልንገድልም ዝግጁ ነን። የኢትዮጵያ ህዝብ ለአንዳርጋቸው አታልቅሱ የጀመረውን ትግል ከግብ አድርሱ ያኔ ነው አንዳርጋቸውን የምታስደስቱት። አንዳርጋቸው ስራውን ጨርሶ ተቀምጧል። ማየት የሚፈልገው ልጆቹን ነው። ሲሉ ተናግረዋል፡፡
10409455_647654315329663_5484929445468543318_n


    የህዝባዊ ሃይሉን ተጠሪ ለማናገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካልንም።

    No comments: