Tuesday, July 8, 2014

አቶ ሀብታሙ አያሌው ተያዙ፤ እስካሁን ያሉበት ሁኔታም ሆነ ቦታ አልታወቀም

July8/2014
ኢህአዴግ በአስቸኳይ ሀብታሙን ሊለቅ ይገባል፤ አለበለዚይም ሁላችንንም ይሰር፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ እስራትንና ሞትን እየፈራ መቁሙ ለ23 አመታት በተናጠል ሲሞት፤ በተናጠል ሲታሰር፤ በተናጠል ሲራዝ፣ ሲራብና ሲጠማ፤ በተናጠል ሲጋዝ አንቀላፍቶ የቆየ ቢሆንም አሁንግን በቃ ብሏል፡፡ መሪዎቹን በማሰር ህዝብን ማጎሳቆል፤ መዝረፍ፤ መጨቆንና ማሰደድ ከአሁን በሁዋላ ይበቃል፡፡
አይደለም እስራትና ለሞት ለባርነትም ቀይተነዋል፡፡ ኢህአዴግ ከታሪክ ይማር! ይህ የሀበሾች ምድር ነዉ፡፡ ጀግንነት ባህላችን ነዉ፤ ባርነት አይዋጠንም፡፡ ለዚህ ደግሞ ኢህአዴግ ከጣሊያን ሊማር ይገባል፡፡ ከባህሪ አባቱ ከሞሶሎኒን ይጠይቀዉ፤ እኛ የሀበሻ ልጆችነን፤ ዉርደት አይዋጥልንም !!!
የፖለቲካ ታጋዮችን በማሰር ትግሉን ማኮላሸት አይቻልም፡፡ ለዚህም የብርቱካን መታሰር ብዙ መጣቶችን ወደ ትግል እንደፋመጣዉ ሁሉ፤ የአንዱአለም መታሰር እነሀብታሙን አምጥቷል፡፡ የብታሙ መታሰር ደግሞ ሺህ ሀብታሙዎችን ያመጣል፡፡
በኛ በኩል ከታሪክ ተምረናል፤ አንድነታችንን አበርትተናል፤ ከዚህ በሁዋላ ኢህአዴግ በልዩነቶቻችን እየገባ እድሜዉን ሊያራዝም አይችልም፡፡ ኢህአዴግም ከታሪክ ይማር እኛ የሀበሻ ልጆች ነን፤ ባርነት ፈፅሞ የማይዋጥልን፤ ጭቆናን አምርረን የምንጠላ፤ በምድር እንደዉሻ ለዘለአለም ከመኖር እንደ አንበሳ አንድቀን በክብር ዉሎ መሞትን እንመርጣለን!!! ምክንያቱም እኛ የሚኒልክ ልጆች ነን!!! እኛ የጣይቱ ልጆች ነን!!! ኢህአዶግ ከታሪክ ይማር!!! ጨዉ ለራስህ ብትል ጣፍጥ፤ አለበለዚያ ድንጋይ ነዉ ብለዉ ይወረዉሩሀል !!! ሀብታሙና የቀደሙት ወንድሞቻችን እነአንዱአለም አራጌ፤ እን እስክንድር ነጋ በአስቸኩዋይ ይፈቱ!!!
ድል የሰፊዉ ህዝብ ነዉ!!!

No comments: