Thursday, September 18, 2014

የበረከት ጤና – ከኢየሩሳሌም አረአያ

September 18,2014
አቶ በረከት ስሞኦን በሳኡዲ አረቢያ የልብ ቀዶ ህክምና እንዳደረጉ ታማኝ ምንጮች አረጋገጡ። በደቡብ አፍሪካ ከአመታት በፊት (ፔስ ሜከር) የተባለ የልብ ምትን የሚያስተካከል በረከት እንደተገጠመላቸው ያስታወሱት ምንጮቹ ይህ በመበላሸቱ ምክንያት የበረከት ህይወት አጣብቂኝ ውስጥ ወድቆ እንደነበረና በቅርቡ አልሙዲ ሳኡዲ ወስደው ይህ እንዲስተካከል በማደረጋቸው የበረከት ጤና ሊመለስ መቻሉን ምንጮቹ አስረድተዋል። በረከት ከጤናቸው ባሻገር በፖለቲካው መድረክ በነስብሃትና ደብረፂዮን በደረሰባቸው መገፋት እንደሚበሳጩ ምንጮቹ አመልክተዋል። በረከት ስሞኦን ለባለሃብቶች በቢሊዮን የሚገመት ብድር በመፍቀድ በከፍተኛ ሙስና ከተነከሩ ባለስልጣናት አንዱ መሆናቸውን የጠቆሙት ምንጮቹ ለአልሙዲና ለሳሙኤል የፈቀዷቸው ብድሮች በቂ ማስረጃ ናቸው ብለዋል። በረከትን ውጭ እየወሰዱ የሚያሳክሙት ደግሞ አልሙዲ ናቸው። በረከት ባለፈው ሳምንት በተካሄደው የፓርቲው ጉባኤ ተካፍለዋል።
bereket

No comments: