Tuesday, January 28, 2014

በኖርዌይ ኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

January 28/2014

ጥር ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- “ባልመረጥነው መጅሊስ  አንተዳደርም!  ያላመንንበትን የሀይማኖት አስተምህሮ አንቀበልም! የህዝበ-ሙስሊሙ የትምህርት ተቋም የሆነው አወሊያ ትምህርት ቤት  በገለልተኝነት ይተዳደር” የሚሉ የመብት ጥያቄዎችን በማንሳታቸው የ አሸባሪነት ክስ የተመሰረተባቸው የሙስሊም አመራሮች ወደ ወህኒ ከወረዱ ከሁለት ዓመታት በላይ ተቆጠሩ።
























ለሁለት ዓመታት ከዘለቀው የፍትህ ሂደት በሁዋላ  በቅርቡ  ለብይን  በተቀጠረው  ችሎት ላይ በብዘዎች ሰንድ ታሳሪዎቹ  በሙሉ ይፈታሉ የሚል ተስፋ የነበረ ቢሆንም፤  አብዘኞቹ እና ወሳኞቹ አመራሮች በፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተብለው እንዲከላከሉ ውሳኔ መተላለፉ፤   የሙስሊሙን ህብረተሰብ ብቻ ሳይሆን  የፍትህና የሰብዓዊ መብት ጉዳይ የሚያሣስባቸውን ሌሎች ወገኖችም ጭምር ያሳዘነ ሆኗል።

ይህ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ከሲህም ባሻገር ለተወሰነ ጊዜ  ከተቃውሟቸው “ፋታ” በመውሰድ  የመሪዎቻቸውን መፈታት በተስፋ ሢጠባበቁ የነበሩትን በርካታ ሙስሊሞች  በማስቆጣት ዳግም  የተቃውሞ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ምክንያት መሆኑ ይነገራል።
ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ላይ  በዋለው ጁምአ፤ በኢትዮጵያ  ከ40 በሚበልጡ ከተሞች  በሚገኙ መስጊዶች ውስጥ  በእስር ላይ የሚገኙ የሙስሊም አመራሮችን ለመሰከር የተዘጋጀው የሰደቃ እና የዱዓ ሥነ-ስርዓት በስኬት መጠናቀቁ ይታወሳል።
ይህቀንበተለያዩ  የውጪአገሮችጭምር የሚኖሩ ሙስሊምና ክርስቲያን ኢትዮጵያውያኖች በአንድነት ሆነው ከፍተኛ ተቃውሞ ያሰሙበት እለት  ነበር። የተቃውሞ መርሐ-ግብሩ፣ ዱአ  (ጸሎት)  በማድረግ፤ ሰደቃ  (ምጽዋት) በመስጠት፣ ስብሰባ በማካሄድ በተቃውሞ ሰልፍና   በተለያዩ የአለም ክፍሎች ተካሂዷል።

በተለያዩ የውጪ አገራት ከተካሄዱት ሰልፎች መካከል-በኖርወይ ዋና ከተማ በኦስሎ የተካሄደውየተቃውሞ ሰልፍ ይገኝበታል።
የሰልፉ አላማ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በተለያዩ እስር ቤቶች ውስጥ የሚገኙ የእስልምና ሀይማኖት መሪዎች፣ ጋዜጠኛችና ፖለቲከኞች  ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ፣ በሀገሪቱ የእምነት ነጻነት እንዲከበርና መንግስት እጁን ከሀይማኖቶች ላይ እንዲያነሳ ለመጠየቅ፣ እንደነበር የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ ገልጿል።

የኦስሎ ሰልፈኛች፣ በ14 ሰዓት ሴንትራል ስቴሺን ፊት ለፊትካለው ከነብር ሀውልት አጠገብ  ከተሰባሰቡ በሁዋላ “ካርል ዮሀን” ተብሎ የሚጠራውን መንገድ ይዘው  ተቃውሟቸውን እያሰሙ ወደፓርላማው ተጉዘዋል።

ሰልፈኞቹ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በማውለብለብ ፣  እንዲሁም የአቡበከር አህመድንና የያሲን ኑሩን ጨምሮ የሌሎች የታሰሩት  የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን ፣የእነ እስክንድር ነጋን፣   የእነ ርዕዮት አለሙን፣ የነበቀለ ገርባን፣ የነ አንዷለም አራጌን፣ የነውብሸት ታዬን እና የሌሎች የህሊና እስረኞችን  ፎቶ ግራፎች በማንገብ  እና መፈክሮችን በማሰማት በ ኢትዮጵያ እየተፈፀመ ያለውን ነገር ለኦስሎ ማህበረሰብ እና ለኖርዌይ ፓርላማ አባላት አሳይተዋል።

ሰልፈኞቹ ኖርዌጂያን ፓርላማ ጋር እንደደረሱ  ከመካከላቸው የተወከሉ ሁለት ኢትዮጵያውያን ወደ ፓርላማው ጽህፈት ቤት በመግባት የተዘጋጀውን ደብዳቤ ለፓርላማው ተወካይ አስረክብዋል።

የደብዳቤው ይዘት በኢትዮጵያ እየቀጠለ ያለው የሰብአዊ መብት ጥሰት ይገታ እና የታሰሩትም የህሊና እስረኞች ይፈቱ ዘንድ  የኖርወይ መንግስት በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ዲፕሎማሲያዊ ጫና እንዲያደርግ  የሚጠይቅ ነው።
በሰልፉ ላይ በኖርዌይ የኢትዮጵያውያን ሙስሊም ተወካይ፣  በኖርዌይ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሊቀመንበር እና የስደተኛች ማህበር ጸሀፊ በየተራ  ንግግር አድርገዋል።

የበረዶው  ቁልል ለአይን የሚያስፈራና የቅዝቃዜውም መጠን ከባድ የነበረ ቢሆንም፤  ሰልፎኛቹ በብርቱ ጽናትና ዲሲፕሊን   ሁሉንም ተቋቁመው ፕሮግራሙን  በታሰበው መልኩ አካሂደዋል።

በሰልፉ ላይ ሙስሊምና ክርስቲያን ኢትዮጵያውያን በአንድ ላይ  እጅ ለእጅ ተያይሰው ከመሳተፋቸውም በላይ፤ “አንድ ህዝብ ነን፣ መቼም መቼም አንለያይም”ሲሉ ተደምጠዋል።



No comments: