Wednesday, January 29, 2014

አብርሃ ደስታ የአረና አባላትን እንዲደበድቡ በሕወሓት የተቀጠሩት አብዛኞቹ ኤርትራውያን እንደሆኑ መረጃ ደረሰኝ አለ

January 29/2014

(ዘ-ሐበሻ) በሕወሓት በደረሰበት ጫና፣ እንግልት፣ እስር እና ድብደባ እንዲሁም የአካባቢው ፖሊስ ለስብሰባው ጥበቃ አልሰጥም በማለቱ ለመሰረዝ የበቃው የአዲግራቱ የአረና ስብሰባን ተከትሎ በቅስቀሳ ላይ የነበሩትን አባላት በሕወሓት ዘንድ በተከፈላቸው ኤርትራውያን እንደተደበደቡ መረጃ ደርሶኛል ሲል አብርሃ ደስታ ከመቀሌ ገለጸ።


“ስሙ እንዲታወቅ ያልፈለገ የዓዲግራት ከተማ ፖሊስ እንደነገረኝ ህወሓቶች የዓረና አመራር አባላትን ለመደብደብ ከተከፈላቸው ወጣቶች አብዛኞቹ ኤርትራውያን ነበሩ።” ያለው አብረሃ ደስታ “ኤርትራውያን ስደተኞቹ በከተማው አስተዳደር የተቀጠሩ ናቸው።” ብሏል።
“ከዓዲግራት ሰዎች ኤርትራውያን ስደተኞች ለገዢዎቹ የተሻሉ ታማኞች ናቸው።” ያለው አብረሃ ህወሓት በተቃዋሚዎች ላይ የሐይል እርምጃ ለመውሰድ የኤርትራ ዜጎችን የመጠቀም ዕቅድ እንዳለው ገልጿል።

“አንድ የከተማው ፖሊስ አዛዥ “ስርዓት አስከብርልን!” የሚል አቤቱታ ስናቀርብለት “ወደኛ ምን ልታደርጉ መጣቹ?” የሚል መልስ ሰጥቶናል።” የሚለው አብርሃ “አሁን የደረሰኝ መረጃ እንደሚያሳየው ግን የፖሊስ አዛዡ ኤርትራዊ ነው።” ካለ በኋላ “ቆይ ግን ይቺ “ትግራይ” የምትባል ክልል የኤርትራውያን ነች ወይ የኢትዮጵያውያን ተጋሩ? እስከመቼ ነው በኤርትራውያን የምንገዛ? እኛ ራሳችን በራሳችን ማስተዳደር አንችልም ማለት ነው? እስቲ በየወረዳው(እስከ ፌደራል መንግስት) ያሉ አስተዳዳሪዎች ከየት እንደመጡ ጠይቋቸው? ከኢትዮጵያ አይደሉም። ከኤርትራ የመጡ ናቸው። በኤርትራውያን ከምንገዛ በራሳችን (ኢትዮጵያውያን) ሰዎች ብንተዳደር ይሻላል።” ሲል ይጠይቃል።

No comments: