Thursday, January 30, 2014

እስር ላይ የሚገኙት የሙስሊሞች ጉዳይ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀጠሮው ተራዘመ

January 30/2014

(ዘ-ሐበሻ) በእስር ላይ የሚጎኙት የሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ዛሬ ጥር 22 ቅነ 2014 ዓ.ም ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ የተገረ ቢሆንም ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ላልታወቀ ጊዜ ቀጥሮው መራዘሙ ታወቀ።

ታህሳስ 3 ቀን 2014 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው የጥፋተኝነት ብይን የተላለፈባቸው እነዚሁ የሙሊሙች ጉዳይ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ለዛሬ ተቀጥረው የነበረው የመከላከያ ምስክር እንዲያቀርቡ የነበረ ሲሆን በውል ባልታወቀ ምክንያት ፍርድ ቤቱ ቀጠሮውን ማራዘሙን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመልክቷል።

አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ቀጠሮው የአፍሪካ መሪዎች ስብሰባን ኢትዮጵያ ውስጥ ስብሰባ ላይ በመሆናቸው ለጸጥታ በሚል ይሆናል የሚል ግምት ቢሰጡም ድምጻችን ይሰማ የተባለው እንስቃሴ ትናንት ባወጣው መግለጫ በዛሬው ፍርድ ቤት ላይ ለቤተሰቦቻቸውና ለጋዜጠኞች ቦታ ለመልቀቅ ሲባል ፍርድ ቤት ተከታዮቹ እንዳይገኙ ጠርቶ ነበር። ለነዚህ የሙስሊሞች ጉዳይ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ የተሰጠው ተለዋጭ ቀጠሮ መቼ እንደሆነ ለማወቅ የተደረገው ለጊዜው ጥረት ባይሳካም ለጠበቆቻቸው ግን ሳይነገራቸው እንደማይቀር ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ ጠቁሟል።

No comments: