Monday, January 27, 2014

ሁለት ከፍተኛ የኦብነግ አመራሮች ከኬንያ በሕወሃት የደህንነት ሃይሎች ታፈኑ::

January 27/2014

የሕወሓት የጸጥታ እና የደህንነት ሰራተኞች አቶ ሱሉብ አህመድ እና አቶ አሊ ሁሴን የተባሉ የኦብነግ ( የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻነት ግንባር ) አመራሮችን ትላንትና ከሰአት በኋላ ከናይሮቢ ከተማ አፍኖ መውሰዱ ተሰምቷል:; እነዚህ የታፈሁ ሁለት አመራሮች ባለፈው ጊዜ ወያኔ በናይሮቢ ከኦብነግ ጋር ባደረገው ምስጢራዊ የድርድር መድረክ ላይ ድርጅታቸውን ወክለው የተሳተፉ እና ለሶስተኛው ዙር ድርድር እየተዘጋጁ ያሉ ነበሩ:: ይህ አፈና የመጀመሪያው ሳይሆን ከዚህ ቀደም በተለያዩ ጊዜያት የሕወሓት የደህንነት ሃይሎች ወደ ኬንያ ዘልቀው በመግባት እጅግ በሚያሰቅቅ እና በኢሰብኣዊ ሁኔታ በሰላም ድርድሮች ላይ የተሳተፉ የተለያዩ የኦብነግ አባላትን አፍኖ በመውሰድ በመግደል ይታወቃል:: በ1998 የሕወሓት ሰራዊት ሶስት የኦብነግ የተደራዳሪ ቡድን አባላትን ገድሎ ሁለቱን በሃይል አፍኖ የወሰዳቸው ሲሆን ከግንባሩ ጋር በተደረገ ድርድር ወደ እብነግ የጦር ሰፈር እንዲመለሱ ተደርጓል::ከሁለት አመት በፊት እንዲሁ በናይሮቢ ከፍተኛ የኦብነግ አመራርን በአደባባይ ገድለዋል:: ምንሊክሳልሳዊ Via ኦጋዴንኔት

No comments: