Friday, January 17, 2014

የፌዴራል ፖሊሲ አጽቢን ቶቆጣጥሯታል ፣ ሕወሃቶች በሕዝቡ ተናደዋል ፣ ህዝቡም ጥያቄዉን አላቆመም (አቡጊዳ )

January 17/2014

የፌዴራል ፖሊሲ አጽቢን ቶቆጣጥሯታል ፣ ሕወሃቶች በሕዝቡ ተናደዋል ፣ ህዝቡም ጥያቄዉን አላቆመም
ከመቀሌ በስተሰምኔ 70 ኪሎሜተር ርቃ በምትገኘው የአጽቢ ከተማ በሕዝቡና በሕወሃቶች መካከል ትላንት የተፈጠረው ዉዝግብ ዛሬም ቀጥሎ ዉሏል። የአካባቢዉ ፖሊስ አቅም በማጣቱ በብዙ መኪና በተለያዩ አቅጣጫዎች፣ ኬሎች አካባቢዎች፣ ተጭነው የመጡ ፌዴራል ፖሊሶች ከተማዋን እንደ ጦር ካምፕ ወረዋታል። ወደ አካባቢዉ የደረሱ የሕወሃት አመራሮች በሕዝቡ ላይ ዛቻን ስድብ እያወረዱበት ነዉ። በሕዝቡ መናደዳቸውን እየገለጹ ነዉ። ሕዝቡ የታሰሩ እንዲፈቱ እየጠቀ ነዉ። ከታስሩት ዉስጥም የ16 አመት ወጣት ይገኝበታል። ወደ ከተማዋ መግባትና መዉጣ አይቻልም። የከተማዋ ነዋሪዎች፣ በየትኛዉም መንግስት እንዲህ አይነት ግፍ አይተን አናውቅም እያሉ ነዉ።
ሰሞኑን የሕወሃት/ኢሕአዴጉ አቶ በረከት ስምኦን፣ ገበሬዉን የፈለገ ነገር ብናደርገዉ የም አይሄዱም በማለት በገዳ ቴሌቭዥኝ (ትንሿ ኢቲቪ) መናገራቸው ብዙዎች እያነጋገረ እንደሆነ ይታወቃል። ነገር ግን በአጸቢ፣ ትግራይ በገበሬዎች ላይ እየተደረገ ያለው አሳዛኝ ግፍ ፣ ገበሬዉ በስፋት በስፋራዉ ተገኝቶ ችግሩን የሚነግርለት ባለመኖር እንጂ ፣ ገበሬዉ ከሃያ አመታት በላይ ግፍ እየተፈጸመበት እንደሆነ በግልጽ ያሳየ ነው።
ከአንድነት ፓርቲ ጋር የቅርብ ግንኙነት ያለዉና ለዉህደትም ጥያቄ ያቀረበዉ፣ የአረና አመራር አባል፣ አብርሃ ደሳት ከመቀሌ ዛሬ አርብ ጥር 9 ቀን በፌስቡክ ያስተላለፈዉን እንደሚከትለው አቅርበናል፡
የአፅቢ ዓመፅ (ክፍል ሰባት)
——————————–
ግጭቱ ቆሟል። መከላከያ ሰራዊት የሃይል እርምጃ ከመውሰድ ታቅቦ ህዝቡ እንዲበተን ተማፅኗል። በፖሊስ የታሰሩትን ነገ (ዛሬ ዓርብ 09/05/06 ዓም) እንደሚፈቱ ቃል ገብቷል። ድርማው ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት (7:00) ላይ ተፈፅሟል። ድርድሩ ዛሬ ዓርብ ይቀጥላል።
የዓመፁ ምክንያት
Basic Cause: የፍትሕ እጦት
የአፅቢ ወንበርታ ወረዳ አስተዳዳሪዎችና ፖሊስ በህዝቡ ጥሩ ስም የላቸውም። አስተዳዳሪዎች የህዝብን የፍትሕ ጥያቄ በአግባቡ ከመመለስ ይልቅ ህዝቡን ማስፈራራት ይቀላቸዋል። ህዝቡ ደግሞ የሚፈራ አይደለም። የወረዳው አስተዳዳሪ ጥያቄ ለሚያነሱ ዜጎች ተቃዋሚዎች እንደሆኑ ይሰብካል፤ ተቃዋሚዎች እንደሚያጠፋም ይዝታል (ህዝብ ሰብስቦ)። ወጣቶች መንግስትን እንዳይቃወሙ ወላጆቻቸውን ያስፈራራል። የፍትሕ ጥያቄ የሚያነሳ ሰው የመንግስት አገልግሎት አያገኝም፤ የፍርድቤት አገልግሎት አያገኝም፣ ፍትሕ ተከልክሏል። የህወሓት አገልጋይ ካልሆነ መሬት አይሰጠውም፣ መስኖ እንዲጠቀምም አይፈቀድለትም። ማዳበርያ እንዲወስድ ይገደዳል፣ ለመውሰድ ፍቃደኛ ያልሆነ ይታሰራል፣ ይሰቃያል። በአፅቢ ወንበርታ የፍትሕ ጥያቄ ማንሳት ክልክል ነው።
ፖሊስም እንደፈለገ ሰው ያስራል፤ ይገድላል። በፖሊስ የተገደሉ የአከባቢው ኗሪዎች አሉ። ፖሊስ ሰዎች አስሮ ይገርፋል። የወረዳው ፖሊስ በህዝቡ በጣም ይጠላል። ባጠቃላይ የአፅቢ ወንበርታ ህዝብ በመንግስት እምነት የለውም። ህወሓትን አይደግፍም። አስተዳዳሪዎቹ ህዝቡን በአሸባሪነት ፈርጀውታል። ህዝቡና አስተዳዳሪዎቹ በፍትሕ እጦት ምክንያት ሆድና ጀርባ ከሆኑ ቆይተዋል።
Immediate Cause: የካሳ ጥያቄ
በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ “ሕኔቶ” ተብሎ በሚጠራ መንደር በመንግስት ባጀት የተገነባ ግድብ አለ። ግድቡ የተቆፈረ ትልቅ የውኃ ጉድጓድ ነው። የውኃ ጉድጓዱ የተቆፈረበት ቦታ ሰፊ የእርሻና የግጦሽ መሬት ነበር። ቁፈራው ሲጀመር ለባለ መሬቶቹ ተገቢ ካሳና ተለዋጭ መሬት እንደሚሰጣቸው በመንግስት ቃል ተገብቶላቸው ነበር። ባለመሬቶቹም በጉዳዩ ተስማምተው ጉድጓዱ ተቆፈረ (ግድቡ ተገነባ)። ለገበሬዎቹ የተገባ የካሳ ቃል ግን አልተተገበረም። መንግስት ቃሉ አጠፈ። ገበሬዎቹ በተደጋጋሚ ጠየቁ። መልስ አላገኙም። የወረዳው አስተዳዳሪዎች ህዝቡን ሰብስበው ምንም ዓይነት የካሳ ጥያቄ እንዳያነሳ አስጠነቀቁት።
ባለ መሬቶቹ መሬት አልባ ሆኑ (በፍትሕ እጦት ምክንያት)። ካሳም አልተከፈላቸውም። ተለዋጭ መሬት ስላልተሰጣቸው የመስኖ ተጠቃሚም መሆን አልቻሉም። በመስኖው እንዲጠቀሙ መሬት የተሰጣቸው የተወሰኑ የስርዓቱ አገልጋዮችና ሌሎች ከግድቡ በመስኖ መጠቀም የሚችሉ (በቶፖግራፊ ምክንያት) የሌላ ቁሸት (ቀበሌ) ናቸው።
በግድቡ ምክንያት መሬታቸው ያጡ ገበሬዎች (ካሳ ያልተከፈላቸው) ልጆቻቸውን ወደ ስዑዲ በመላክ ይተዳደሩ ነበር። አሁን ይጠውሯቸው የነበሩ ልጆቻቸው አብዛኞቹ ከስዑዲ ተመልሰዋል። መሬት ወይ ካሳ ይፈልጋሉ። እንደገና ጥያቄው ተነሳ። አስተዳዳሪዎችም “አርፋቹ ተቀመጡ፤ አለበለዝያ ከዚህ እናጠፋችኋለን። ለተቃዋሚዎች (ጥያቄ ለሚያነሱ ማለት ነው) ቦታ የለንም። ጥያቄም አናስተናግድም” የሚል የማስፈራርያ መልስ ተሰጣቸው።
ጥያቄ የሚያነሱ ገበሬዎች ከግድቡ መስኖ ከሚጠቀሙ ገበሬዎች ጋር በጉዳዩ ተወያዩ። “መንግስት ካሳ ይክፈለን፤ እናንተም ከኛ ጋር ጠይቁ። አግዙን ወይም ደግሞ እናንተ ካሳ ክፈሉን” የሚል ሐሳብ አነሱ። ምክንያቱም ግድቡ ያለው በሰዎች መሬት ላይ ነው። ባለመሬቶቹ ተመልካቾች ሌሎች ተጠቃሚዎች የሚሆኑበት ሁኔታ ፍትሐዊ አይደለም የሚል የክርክር ሐሳብ ተነሳ። ባለ መስኖዎቹም በካሳ ጥያቄው ተስማምተው መንግስት ለገበሬዎቹ ካሳ መክፈል እንዳለበት ሐሳብ ቀረበ።
አስተዳዳሪዎችም ካሳ እንደማይከፍሉ አረጋገጡ። ህዝብ ካመፀ የሃይል እርምጃ እንደሚወስዱ አስጠነቀቁ። ባከባቢው የነበሩ አስራ አምስት ምልሻዎች ትጥቃቸው በሃይል እንዲፈቱ ተደረገ። ግጭት እንደሚነሳ ታወቀ።
የ ሐሙስ ዓመፅ
ካሳና ተለዋጭ መሬት የተከለከሉ ገበሬዎች ዓመፅ ጀመሩ። ዓመፁ የተጀመረው “ግድቡ በመቆጣጠር” ነበር። መፍትሔ እስኪገኝ ድረስ በግድቡ የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ (የመስኖ ስራ ጨምሮ) እንዲቆም አደረጉ። “ግድቡ መሬታችን ነው፤ ተገቢውን ካሳ ካልተሰጠን ዉኃችን አንሰጥም” አሉ። ግድቡን ለማስለቀቅ የፖሊስ ሃይል ተላከ። ዓመፁና ግርግሩ ተጀመረ። ፖሊስ መቆጣጠር ስላልቻለ መከላከያ ሰራዊት ገባ።
ስለዚህ የዓመፁ መነሻ የፍትሕ እጦት ነው። መንግስት የገባውን ቃል ባለማክበሩ የተፈጠረ ዓመፅ ነው።
አሁን ከወረዳ አስተዳደሩ የደረሰኝ መረጃ እንደሚያመለክተው የወረዳው አስተዳዳሪዎች የህዝብ ዓመፅ ከሽብርተኝነትና ተቃዋሚ ፓርቲዎች (ዓረና) ጋር በማገናኘት ዜጎችን ለማስወንጀል ተዘጋጅተዋል። ሌላኛው ዕቅድ ደግሞ ህዝቡን ለመከፋፈል ያለመ ስትራተጂ እየቀረፁ ነው (መስኖው የሚጠቀምና የማይጠቀም በማለት ለሁለት ሊከፍሉት ነው)። በአንድ በኩል ለዓመፁ ተቃዋሚ ፓርቲን ተጠያቀ ማድረግ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በመስኖው የሚገለገሉ ገበሬዎች ከአስተዳዳሪዎቹ ጎን እንዲሰለፉና ህዝቡ እንዲከፋፈል ለማድረግ እያሴሩ ነው። ከተሳካላቸው ህዝብ ከህዝብ ጋር በማጣላት እነሱ ከሐላፊነት ለማምለጥ መመኮራቸው አይቀርም። ህዝብ ይህን የህወሓት ከፋፋይ ስትራተጂ ነቅቶ መጠበቅ አለበት። (እኛን ያልደገፈ መስኖ አይጠቀምም በማለት መስኖ ተጠቃሚዎቹ በ አስተዳዳሪዎች ጎን ለማሰለፍ ጥረት ሊያደርጉ ይችላሉ)።
ዓርብ 09/05.06 ዓም ከጠዋቱ 3:05 ተፃፈ
የአፅቢ ዓመፅ (ክፍል ስምንት)
—————————–
ህዝቡ እየተሰባሰበ ነው፣ የፌደራል ፖሊስ እየገባ ነው
አከባቢው በመከላከያ ሰራዊት ቁጥጥር ስር ይገኛል። የአፅቢ ወንበርታ ህዝብ (ሕነይቶ) በፖሊስ የታሰሩትን ወገኖቹ ለመቀበል ባከባቢው እየተሰባሰበ ነው። የተያዙትን ሰዎች ግን እስካሁን ድረስ ባከባቢው የሉም። በነሱ ምትክ ብዙ የፌደራል ፖሊሶች አከባቢውን (ከመከላከያዎች ጋር በመሆን) እየተቆጣጠሩት ይገኛሉ።
ትናንት በፖሊስ ተይዘው ወዳልታወቀ ስፍራ የተወሰዱ ያከባቢው ኗሪዎች ብዛታቸው በዉል አይታወቅም። ህዝብ እያየ ፖሊስ እየደበደበ የወሰዳቸው አራት ሰዎች ግን የሚከተሉ ናቸው።
(1) ታደሰ ሃይሉ
(2) አሰፋ ካሕሳይ
(3) ገብረእግዚአብሄር ገብረሚካኤል
(4) የአቶ ግርማይ ግብረየሱስ ልጅ (የ16 ዓመት ወጣት) ናቸው።
የአፅቢ ወንበርታ ህዝብ በታሪክ ይህን ያህል ግፍ ያደረሰበት መንግስት እንዳልነበረ አስተያየት ሰጪዎች እየተናገሩ ነው። አስተያየት ሰጪዎቹ ለመብት ጥያቄ ይህን ያህል ግፍ መፈፀም አግባብነት የለውም ይላሉ።
የተፈጠረ አዲስ ነገር ካለ አቀርባለሁ።
(ዓርብ ጠዋት ከረፋዱ አምስት ሰዓት ነው የተፃፈው)።
የአፅቢ ዓመፅ (ክፍል ዘጠኝ)
ህዝቡ እንዳይንቀሳቀስ በፌደራል ፖሊስ ተከቧል
———————————————
አሁን ዓርብ ከጠዋቱ አምስት ሰዓት ተኩል ነው። ዓመፁ ወደ ሌላ አከባቢ እንዳይሰፋ በመፍራት የፌደራል ፖሊሶች አከባቢው ከበውታል፤ ህዝቡም በፖሊስ ተከቧል። የፖሊስ አዛዦች ህዝቡን እያስፈራሩ ይገኛሉ። ህዝቡም መብቱ እንዲከበርለትና ታፍነው የተወሰዱ ወገኖቹ (ትናንት ማታ በተገባላቸው ቃል መሰረት) እንዲፈቱ እየጠየቀ ነው። አከባቢው ግን ተከቧል። ካከባቢው መውጣትና ወደ አከባቢው መግባት ተከልክሏል። አንድ ባህረ ገብሩ የተባለ ያከባቢው ኗሪ ካከባቢው ወደ አፅቢ ከተማ ሲጓዝ በፖሊስ ታፍኖ ወዳልታወቀ ቦታ ተወስዷል።
ህዝቡ ታፍነው የተወሰዱ ያከባቢው ኗሪዎች ፖሊስ ይደበድባቸዋል፣ ይገድላቸዋል በሚል ስጋት ተጨናንቀዋል። ሳይፈቱም ህዝቡ እንደማይበተን አስታውቀዋል። የፖሊስ ማስፈራርያው ግን አይሏል። ባከባቢው በዜጎች ላይ ግፍ ሲደርስ የተለመደ በመሆኑ የተያዙት ሰዎች ድብደባና ግድያ እንደሚጠብቃቸው ይገመታል።
ባከባቢው (አፅቢ ወንበርታ) እስካሁን ድረስ (ከዚህ ቀደም ማለት ነው) ታደሰ ጊደይ አባዲ የተባለ የሩባ ፈለግ ኗሪ በመንግስት አካላት በጥይት ተገድላል። የአቶ ገብረሂወት (ስሙ ለግዜው አልያዝኩትም) ልጅም በመንግስት አካላት በጥይት ተመቶ ህይወቱ አልፏል። አቶ ገብረሚካኤል ተስፋይ (ጣብያ ፈለገወይኒ)፣ አቶ ታደሰ መዝገቦ (ጣብያ ሩባ ፈለግ)፣ አቶ ህይወት አባይ (ጣብያ ሩባ ፈለግ) ወዘተ በፖሊስ ድብድባ (ቶርቸር) እንደደረሰባቸው ታውቋል: ከፍተኛ የስነ ልቦና ጉዳት ደርሶባቸዋል።።
ከዚህ በመነሳት ታፈነው በተወሰዱ ዜጎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የህዝብ ቅሬታ አለ። ፖሊስ ግን ህዝቡን ከቦ አላንቀሳቅስ ብሏል።
(በ 5:55 ተለጥፏል)።
የአፅቢ ወንበርታ ህዝባዊ ዓመፅ (ክፍል አስር)
የህወሓት አመራር አባላት ባከባቢው ይገኛሉ
————————————
አከባቢው በብዙ የወረዳና የክልል ፖሊሶች፣ የፌደራል ፖሊሶችና መከላከያ ሰራዊት ተከቦ ህዝቡም እንዳይንቀሳቀስ ታግቶ በመከላከያ ሰራዊት የታጀቡ የዞንና ክልል አስተዳዳሪዎች (የህወሓት ባለስልጣናት) ህዝቡን እያነጋገሩ ነው። ባለስልጣናቱ ህዝቡ ዓመፁ የቀሰቀሰው ማን እንደሆነ፣ ለምን የሃይል መንገድ መጠቀም እንደመረጠ ወዘተ በማስፈራራት እየጠየቁ ነው። ህዝቡም የመሬቱ ካሳ ወይ ተለዋጭ መሬት የማግኘት መብቱ እንዲከበርለት፣ ታፍነው የተወሰዱ እንዲፈቱ ይጠይቃል። መግባባት የለም። የህዝቡ ጥያቄ ያናደዳቸው አስተዳዳሪዎች ህዝቡ ትናንት የቀሰቀሰው ዓመፅ “ስህተት” መኖሩ ካላመነ ወደ ቤቱ እንዲሄድ እንደማይፈቅዱለት እያስፈራሩት ነው። ህዝቡ በሃይል ዓፍነው ይዘውታል (በፀጥታ ሃይል ብዛት)። የኢህአዴግ የደህንነት ሰዎች እዛው ይገኛሉ። ካከባቢው ለመውጣትና ወደ አከባቢው ለመግባት የሞከሩ የአከባቢው ኗሪዎች እየታሰሩ ነው። እስካሁን ሰባት ሰዎች ታስረዋል (አንድ ሃፍቱ ገብረመድህን የተባለ የቀድሞ የመከላከያ ሰራዊት አባል ጨምሮ)።
ዓርብ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ተኩል ተፃፈ።
የአፅቢ ወንበርታ ህዝባዊ ዓመፅ (ክፍል አስራ አንድ)
————————————
-
ትልቁ ኪሳራ
የትናንትው የአፅቢ ወንበርታ ህዝባዊ ዓመፅና የፖሊሶች ተኩስ (የነበረውን አጠቃላይ ግጭት) በካሜራና በሞባይል ሲቀርፁ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ። የግጭቱ ሙሉ ሂደት ቀርፀው ለህዝብ ለመበተን ዉቅሮ ከተማ ሊገቡ ሲሉ በልዩ የህወሓት የደህንነት ሃይሎች ተይዘዋል። ታፍነው ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደዋል። ሞባይላቸውና ካሜራቸው ተነጥቀዋል። ህወሓቶች የአፅቢ ወንበርታ ህዝብ በደልና ዓመፅ ሌሎች ህዝቦች እንዳይሰሙት ለማፈን በማቀድ ቪድዮውን ይዘውታል። መረጃው መበተኑ ግን አይቀርም። ለኔ ግን ትልቅ ኪሳራ ነው።
ይህን የተደረገው ዓርብ 09/05/06 ዓም ከቀኑ ስምንት ከአርባ (8:40) ነው።
አቡጊዳ 

No comments: