Sunday, January 19, 2014

ርዮት አለሙ ጡቷ ላይ ቱመር አለ፣ ግን ክትትል አላገኝችም !

January18/2014

ሴፍ ዎርልድ ፎር ዎማን ( safe world for women) የተሰኘው ለሴቶች መብት የሚሟገተዉ ድርጅት፣ ርዮት አለሙ እንድትፈታ የሚጠይቅ ፔትሽኖች እያስፈረመ ነዉ። ድርጅቱ, የርዮት አለሙ አባት አቶ አለሙ ጎቤዶን በመጥቀስ እንዳስቀመጠዉ፣ ርዮት አለሙ፣ በአንድ ጡቷ ላይ ቱመር ያለ ሲሆን ፣ ከጡቷም ደም እንደሚፈስ ይገልጻል።
ያለችበት ሁኔታ ክትትል የሚያስፈለገዉ ቢሆንም፣ ክትትል እያደረገች እንዳልሆነ የገልጹት አቶ አለሙ፣ የልጃቸው ጤንነት ሁኔታ በጣም እንዳሳሰባቸው ይናገራሉ።
ርዮት አለሙ በከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ እንግሊዘኛ አስተምራ እንደወጣች ሲሆን በአገዛዙ ደህንነቶች የተያዘችው፣ ከተያዘች ከሁለት አመት ከስደስት ወራት አልፏታል።

No comments: