Monday, August 18, 2014

አቶ ብርሃኑ በርሀ የዓረና ትግራይ ፓርቲ ሊቀ መንበር በወቅታዊ የሀገራችን ጉዳይ ላይ ለ ሎሚ መፅሄት የሰጡት ቃለ መጠይቅ

Augest 18/2014
ሎሚ* ለመሆኑ አሁን ፓርቲያችሁ በምን አይነት ሁኔታ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል?


አቶ ብርሃኑ በርሀ የዓረና ትግራይ ፓርቲ ሊቀ መንበርአቶ ብርሃኑ:- ፓርቲያችን ዓረና ትግራይ የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች የፓቲርው ጠቅላላ ጉባኤ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ተግባራዊ ማድረግ መሰረት ያደረገ ሆኖ ጠቅለል ብሎ ሲገለፅ የዓረና አማራጭ ፖሊሲና በወቅታዊ ሃገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ያለው አ ም ለህዝብ በማስተዋወቅ የአረና አማራጭ ፖሊሲዊች የህዝቡ አጀንዳና የፍላጎቱ መገለጫ ሆነው ከፓርቲ ፖለቲካ ወደ የህዝብ ፖለቲካ በማሸጋገር የነፃና ፍትሃዊ ምርጫ እድል ተፈፃሚነት በህዝቡ የነቃ ተሳትፎ ዋስትና እንዲያገኝ ለማስቻል ተከታታይ የህዝብ ፖለቲካዊ ስብሰባዎች ማካሄድ ፣ አማራጭ ፖሊሲያችን በማስተዋወቅ የምንፈጥረው ተቀባይነትና ድጋፍ የፈጠረልን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ፓርቲያችን በአባላትና በደጋፊዎች ብዛት እንዲሁም በአደረጃጀት መዋቅራችን በማስፋት እራሳችንን ለሰላማዊ ፣ሕጋዊና ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ውድድር ብቁ ሆኖ መገኘትን ያለመ ነው ፡፣ የዓረና አማራጭ ፖሊሲ የህዝቡ አጀንዳ ሆኖ ህዝቡ ይጠቅመ’ል የሚል ግንዛቤ ወስዶ የራሱ አጀንዳ አድርጎት ለውጤታማነቱም ወሳኙ ራሱ ህዝብ መሆኑን እንዲገነዘብና ያን ለማድረግ ህዝብ ብቃቱም ችሎታውም እንዳለው እንዲገነዘብ ማስቻል የፖለቲካ ስራችን አቅጣጫና የሰላማዊ ትግላችን ስትራተጂ መመርያም በተግባር ለመፈፀም ነው የምንንቀሳቀሰው፣፣

 ሎሚ* ዘመቻ አብርሃ ደስታ ብላችሁ ያዘጋጃችሁት ፕሮግራም እንዴት ነበር?  

አቶ ብርሃኑ:- አብርሃ ደስታ ሀገራዊ ራኢ ከሰነቁና የአረና አመራር ወራሾች ይሆናሉ ተብለው ከምንገምታቸው ንቁ የአረና ወጣት አመራሮች አንዱ ነበር፡፣ አካዳሚያዊና ፖለቲካዊ ብቃቱ ተስፋ የሚጣልበት መሆኑን በተግባር አሳይቶአል ፣ ለማነበት ራኢ ግብራዊነት የማይታጠፍ የፀና አ ም አሳይቶአል ፣ አጠቃላይ ፖለቲካዊ ስብእናውና የመቀስቀስ ችሎታው የሚደነቅ ነው፣ የኤሌክትሮኒክስ ቴክኒዮሎጂ በመጠቀም የፌስቡክ ንጉስ እስኪመስል ሰርቶአል ፣ አስተምሮአል አሳምኖአል ተደናቂነትም አትርፎአል፣ ይህ በመሆኑ ለአብርሃ ደስታ ብቻ ሳይሆን ውለታና ምስጋና ለሚገባቸው ወጣት መሪዎች ክብርና አድናቆታችን ለመግለፅ ከመታሰሩ በፊት ህዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባ እንዲካሄድባቸው አብሮን ውሳኔ የሰጠባቸው የራያ አዘቦ ወረዳ አከባቢ ያካሄድነው ህዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባ ዘመቻ አብርሃ ደስታ ብለናቸዋል ፣
[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—

No comments: