Monday, August 4, 2014

“እኛ አባቶች ከእንግዲህ ሀላፊነት ለወጣቶች በመስጠት በምክርና የተለያየ ተሞክሯችን በመስጠት ከጎናቸው መቆም አለብን፣

August 4/2014
hqdefault
በቅርቡ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር ለመሆን በዕጩነት ቀዳሚ ሆነው ማለፋቸው የፓርቲው ልሳን የሆነው ፍኖተ ነጻነት አስታውቋል፡ ፡በዚህ ጉዳያ ያልተናደደና ያልተበሳጨ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ይኖራል ብሎ መገመት ይከብዳል፡፡ በተለይ ያእቆብ ሀ/ማሪያም በግንቦት 25/2005 በሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ ላይ በኩባ አደባባይ ለሰልፈኛው አቅርበውት በነበረው ንግግቸው ላይ “እኛ አባቶች ከእንግዲህ ሀላፊነት ለወጣቶች በመስጠት በምክርና የተለያየ ተሞክሯችን በመስጠት ከጎናቸው መቆም አለብን፣ከእንግዲህ የእኛ ሀላፊነት ወንበሩን ለወጣቱ ለአዲሱ ተውልድ መልቀቅ ነው፣ “ብለው ነበር፡፡ ኢንጂነር ግዛቸው ግን እንዲህ ቅዱስ ነገር ለመስማት ፍላጎትም ያላቸው አይመስልም፡፡ ኢህአዴግም የእሳቸው ወደ ፊት መምጣት እንደ ሰማይ መና የሚቆጥረው ነገር ነው፡፡ ለምን? ፣ሰውዬው ታሰረው ከነበሩትና በኋላም በይቅርታ ከተለቀቁት የቅንጅት አመራሮች አንዱ ነበሩ፡፡እና ምን አለበት ሊባል ይችላል፡፡በጣም ከባድ ችግር ነው ያለበት፡፡ዋናው ነገር ምን አይነት ይቅርታ ጠይቀው ነው የወጡት የሚለው ነው፣ እንዲህ የሚል ነው
….ህገ መንግስቱንና ህገመንግስታዊ ስርአቱን በሀይልና በአመጽ ለመናድ በህገወጥ መንገድ ተንቀሳሰናል በዚህም ምክንት ብዙ ጥፋትና ውድመት ተከስቷል፤እንዲህ አይነት ነገሩ ውስጥ በማድረግ ህዝባችንና መንገስታችንን በመበደላችን አጥፍተኛል ተጸጽተናል፣ከእንግዲህም አይለመደንም ይቅርታ ይደረግልን… የሚል አይነት ነበር፡፡
ኢህአዴግ በእንዲህ አይነት ሁኔታ ይቅርታ እንዲጠይቁ ያደረገው በትክክል የተባለው ነገር ስለፈጸሙ ሳይሆን፣፣ከእስር ትፈታላችሁ ነገር ግን ካሁን በኋላ እኔ ከምላችሁ አንዳች ፍንክች ብትሉ ተመልሳችሁ ትገቧታላችሁ ማለቱ እንደሆነ ትርጉሙ ግልጽነው፡፡ለዚህም የብርቱካን ሚደቅሳ ነገር ማየት ረዘም ተደርጋ እንዳተሰረች ዶሮ እንጂ እኝደወፍ እንድትበር አልተፈቀደላትም፡፡ስዊድን ሀገር ሄዳ ኢህአዴግ የማይፈቅደው ነገር ተናግራ ወደ ሀገር ቤት ስትመጣ ብዝብ ፊት ይቅርታ ጠይቂ አለበለዛ በተስማማስ መሰረት ወደነበርሽበት ትመለሻለሥ ጠባለች፡፡እምቢ አለች፡፡ተመለሰች፡፡በወቅቱ አብዛኛው የአንድነት አመራሮች በፊርማ የወጡ ስለነበሩ ለምን ብለው ሊከራከሩላት አልቻሉም፣እንዳውም የሚሉሽን አትሰሚምና የእጅሽን ነው ያገኘሽው በሚል አይነት ሁኔታ በብዙ መንገድ ሊኮንኗትና ሊያሳጧት ሞክረዋል፡፡
በወቅቱ ደግሞ ድርጅቱን በሀላፊነት ይመሩ የነበሩት ዛሬ ቲፎዞ አሰልፈው የመጡት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው ነበሩ፡፡እኚህ ሰው በወቅቱ ብርቱካን የታሰረችው እስርቤት የገባችውን የፊርማውን ቃል ስላቃለለች ነው የሚል በሚመስል የብርቱካንን ስም የሚያነሳ ሁል በድንጋይ ሳይቀር እስከማስደብበብ ደርሰዋል ውሸታም የሚለኝ ያ አይመስለኝም፡፡ከድርጅቱ አግደዋል አባረዋል፡፡ለዚህም የዛሬዎቹ የሰማያዊ ፓርቲ መሪዎችና አባላትን መጥቀስ ይቻላል፡፡ሰውዬው ድርጅቱን ይመሩት እስርቤት የፈረሙትንነገር በህልማቸውና በቅዠታቸው እየመጣባቸው ነበር፡፡ ለኢህአዴግ የገቡትን ቃል ለማክበር ብዙ የደርጅቱን ወጣቶችና ስም አባክነዋል፡፡ዘሬም ያ ፍርሀታቸው ደብቀው በፍርሀት ሊመሩት ከነቲፎዟቸው ብቅ ብለዋል፡፡በነገራችን ላይ ይህ ሰው በ97 ምርጫ ወቅት ፓርላማ እንግባ አንግባ በሚባልበት ወቅት እንግባ (ኢህአዴግ የሰጠንን ተቀብለን እንግባ) ብለው ይከራከሩ የነበሩ ከዚህም የሀገር ፍቅር ይኖራቸው ይሆናል እንጂ ወደፊት ገፍቶ ኢህአዴግን ለመታገል የሚጎላቸው ነገር እንዳለ ማወቅ ይቻላል፡፡ለጫማው በኋላ ይታሰብበታል ላሁኑ ማምለጥ ነው የሚሉ አይነት ሰው ናቸው፡፡
እና ምን ለማለት ነው ? ሰውዬ የአንድነት መሪ ቢሆኑ ድርጅቱን የሚመሩት ያኔ በፈረሙት ፊርማ ታስረውና ተሸብሽበው ነው፡፡አንዷል አተራጌ አፌን ሞልቼ ስለነጻነት አወራለሁ ሲል አትችል እንዲህ ማድረግ እንደማትችል እስርቤት ፈርመሀል ተብሎ ይኀው የትእንዳለ እናውቃለን፡፡ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ የፈረው ፊርማ በሀገር ቤት የትም እንደማያደርሰው አውቆ ይኸውየት እንዳለ እናውቃለን፣እዛም አልቀረለትም የሞት ፍርድ ተፈርዶበታል፡፡ዶ/ር ያእቆብ ቃሊቲ እያለሁ የፈረምኩት ፊርማ እያሰብኩኝ የኢትዮጵያን ህዝብ ትግል ከምጎዳ አርፌ ብቀመጥ ይሻላል ብለው ይመስላል ይኸው መሪ አይደለም የየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባልም አይደሉም፡፡ብርቱካንም በውሸት ታስራችሁ በተጭበረበረ መንገድ የፈረማችሁት ፊርማ እፈራችሁ የምትኖሩ ከሆነና ሌላውም ሲታሰር ፍርዳችሁና ና ምላሻችሁ ይሄ ከሆነ ብላ ሀገሩም ትግሉም ጥላ ተደብቃ እየኖረች ነው፡፡
ኢንጂነር ሀይሉሻውል መለስን ጎንበስ ብለው እጅ ነስቻለሁ ያሉት ወደው አይደለም፣ የፈረሙት ፊርማ ምን ያህል ቀልባቸውና ቅስማቸውን እንደሰበራቸው መገመት ይቻላል፡፡ያኔ ታስረው የነበሩ ጋዜጠኞች ሀገር ጥለው ያሉት ቃሊትን ብቻ ሳይሆን የፈረሙትንም ፊርማ ስለሚፈሩ ጭምር ነው፡፡ኢህአዴግ ሰማያዊ ፓርቲ በአደረጃጀትም ሆነ በዐጣቃላይ ጥንካሬ ከአንድነት ስለሚበልጠው አይደለም እንዲህ ልቡ የተሸበረው፣የቀሊቲን ፊርማ እያሰቡ የሚመሩ ሰዎች ስላልሆኑ ጭምር ነው፡፡
ስለዚህ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው የአንድት መሪ ሆኑ ማለት ድርግቱ ክንፍ ብቻ ያለው የማይበር የታሰረ ዶሮ ከመሆን ውጪ ምንም አያመጡም፡፡ ስለዚህ በገዛ ፈቃዳቸው በቃኝ ብለው ከጎን ሆነው የትግል ልዳምቸውና ምክርብቻ ማካፈል አለባቸው፡፡ ደግሞም ባለፈው 22 ውስጥ ፖለቲካ ውስጥ ብዙ ጊዜጣቸውን ያሳለፉት እንደ በየነ ጴጥሮስና ዶ/ር መራራ ጉዲና በድርጅት አመራርነት በተለያየ ቦታ ተለጥፈው ተጣብቀው ነው ነው፡፡ለኢህአዴግ የጣሉት እንጂ ያስጣሉት ነገር የለም፡፡ሸክም መሆን ብቻ፡፡መአድ ውስጥ አመራር ውስጥ ነበሩ፣መኢአድ ውስጥ እንዲሁ፣ቅንጅት ውስጥ የታሰሩት አመራር ላይ ስለነበሩ ነው፣አንድነት እሰካሁን የሚያሳማውን ስም ያሰጡትም አመራር ላይ ስለነበሩ ነው፡፡አይተናቸዋል ፣በቃ አሁን ቦታውን ለሌላ ይልቀቁ!!በተለይ የእሳቸው ወደ ስልጣን መምጣት ድርጅቱን እንደእነ ቡልቻ ባሉ “የበራላቸው” ሰዎች በብሄር (በተለይ መዐአድ ውስጥ የነበሩ ሰው ከመሆናቸው አንጻር)በጣም የሚያሳማና ኢህዴግም የያኔው አንዳንድ የቅንጅት ስህተቶችን እያነሳ ህዝብ የሚያስትበት አጀንዳና የትግል መግደያ ከመሆን አያልፉም!

No comments: