Tuesday, August 5, 2014

አዲስ መረጃ በአቶ በረከት ዙሪያ፡ ምስጢር አወጡ የተባሉትን የጂዳ ቆንስላ ጽ/ቤት እያመሰ ነው

August5/2014
ሰበር ዜና አቶ በረከት ስሞኦን ዛሬ August 5, 2014 የሆስፒታል ቀጠሮቸውን ያጠናቅቃሉ !
« በአቶ በረከት ጉዳይ ካድሬዎች ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤትን ሲያምሱ ዋሉ »
bereket alamudi demeke
ሳውዲ አረቢያ በህክምና ላይ የሚገኙት አቶ በረከት ስሞኦን ከህመማቸው አገግመው ሼክ አላሙዲን ወደ አዘጋጁላቸው ሚስጥራዊ ሆቴል ካቀኑ ወዲህ እኚህ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን ስላሉበት የጤነነት ሁኔታ በእርግጠኝነት መናገር ባይቻለም ከሁለት ቀን በፊት የሼክ አላሙዲን ወደ አሜሪካ ማቅናት ተከትሎ የአቶ በረከት ስሞኦን የ ጤንነት ሁኔታ በመላካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ መረጃዎች ያመላክታሉ ። አቶ በረከት ስሞኦን እስካሁን ሳውዲ አረቢያ ከሚገኙ ዲፕሎማቶች ጋር በስልክም ሆነ በአካል እንዳለተጋናኙ የሚገልጹ እነዚህ ምንጮች እኚህ የመንግስት ከፍተኛው ባለስልጣን ያረፉበት ሆቴል ምሲጥራዊነቱ በከፍተኛ ጥንቃቄ የተጠበቀ መሆኑን ይናገራሉ።
የአቶ በረከት የጤንነት ሁኔታ በማህበራዊ ገጾች መነጋገሪያ ከሆነ ወዲህ ጭቀት ውስጥ የገቡት ሼክ አልሙዲን የተለያዩ ሆቴሎችን እየቀያየሩ እኚህን የመንግስት ባለስልጣን ደብቀው ሲያስታምሙ እና አሰፈላጊውን ድጋፍ ሲያደርጉላቸው መክረማቸውን ለማውቀ ተችሏል። አቶ በረከት ከሆስፒታል ከወጡ ወዲህ የተለያዩ ሆቴሎች እንዳረፉ የሚገልጹ መረጃዎች ሼኩ ወደ አሜሪካ ከማቅናታቸው በፊት በግል ከተከራዩላቸው ምርጥ ሆቴሎች ምናልባተም የመጨረሻ የአቶ በረከት ሚስጥራዊ ማገገሚያ ይሆናል ተብሎ ከሚነገርለት ሆቴል ነገ ወደ «ቡግሻን» hospital በማቅናት የመጭረሻ የህክምና ቀጠሮአቸውን ካጠናቀቁ በሃላ በአጭር ቀን ውስጥ፡ ወደ ሃገር ይመለሳሉ ተብሎ ይጠበቃል። በተያያዘ ዜና በህክምና ላይ የምትገኘው የ6 አመቷ የአቶ በረከት ልጅ ህጻን ህሊና በረከት በመልካም ጤነት ላይ መሆኗን የኢትዮጵያ ሃገሬ የሆስፒታል ምንጮች አረጋግጠዋል ።
ይህ በዚህ እንዳለ በጅዳ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ካድሬዎች የአቶ በረከትን ገበና አጋለጣችሁ በሚል ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ዛሬ የመጡ ኢትዮጵያውያን ሲያዋኩቡ መዋላቸው በጅዳ እና አካባቢው ኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተናኛ ቁጣን ማስነሳቱ ን ለማረጋገጥ ተችሎል ። ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት የተለያዩ ጉዳዮቹን ለማስፈፀም በጠራራ ጸሃይ ሲነፍሩ የነበሩ ኢትዮጵያዊያንን እንደ ዜጋ አዝነው በአግባቡ ከማስተናገድ ይልቅ አቶ በረከት መታመማቸውን መረጃ ያወጣችሁት እናንተ ናችሁ የተቃዋሚ ወሬ አቀባዩች እናተን ሰብስቦ ማቃጠል ነበር በሚል ዛቻ ፍጹም ኢትዮጵያዊ ነኝ ከሚል የድርጀት አባል በማይጠበቅ ቃላት በኢ.ህ.ዴ.ን ካድሬዎች እና የህወሃት ካድሬዎች ሲያዋክቡ ሲዋከቡ መዋላቸውን በደሉ የተፈፀመባቸው ወገኖች ገልፀውልናል። በተለይ እራሳቸውን ብቸኛ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ፈላጭ ቆራጭ አድርገው ያስቀመጡት የህወሃት የቀድሞ ታጋይ አቶ ገሬ እና መዝገብ ቤት ሃላፊ የሆነው የትግራይ ተወላጁ የቀድሞው የህወሃት ታጋይ አቶ ሽፋ ባለጉዳዮችን ሲያንገራግሩ ከነበሩ መሃከል ግንባር ቀደም እንደነበሩ ታውቋል።
የጅዳ ቆንስል ሃላፊ የነበሩትን ቆንስል ዘነበን በተጽዕኖ ያስነሱት እንዚህ የጅዳ ኢህአዴግ ካድሬዎች የጅዳን ቆንስላ ጽ/ቤት በመቆጣጠር ደካማ ዲፕሎማቶችን በመናቅ እንዳሻቸው በማድረግ ከማድረጋቸውም በላይ ለጉዳይ የመጣውን ኢትዮጵያዊ ማጉላላት እና ፓስፖርት እስከ መንጠቅ የደረሱ ወንጀለኞች መሆናቸው በአብዛኛው የጅዳ ማህበረሰብ ዘንድ ይነገራል። ከዚህ መሰሪ ተግባራቸው ያልታቀቡት እንዚህ ግለሰቦች የአቶ በረከትን ለህክምና መምጣትን መረጃ አወጣችሁ የሚሏቸውን ወገኖች ወደ ቆንስላው ግቢ ሲገቡ በመተናኮል ሁከት ቀሰቀሱ ብለው ለማሳሰር በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ከጽ/ቤት የወጡ መረጃዎቻችን ጠቁመዋል።
Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ

No comments: