Thursday, August 7, 2014

መከሰሳቸውን ከፖሊስ ሳይሆን ከሚዲያ የሰሙት የሎሚ መጽሔትና የአፍሮታምይስ ጋዜጣ አዘጋጆች ይናገራሉ

Augest 6/2014
“ስለመከሰሳችን የምናውቀው ነገር የለም”
አቶ ግዛው ታዬ
የሎሚ መፅሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር
ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ
ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ
ክሱን በተመለከተ የምናውቀው ነገር የለም። ከዚህ በፊት ከማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ይደወልልን ነበር። እዚያ ሄደን ቃላችንን እንሰጥ ነበር።
እኛ አሁን መገረም ነው የፈጠረብን። ሕገ-መንግስቱን አከበራለሁ የሚል መንግስት በምን መልኩ ነው የክስ ዝርዝር ሳይደርሰን፣ መጥሪያ እጃችን ላይ ሳይገባ በመገናኛ ብዙሃን ክሳችንን የሚያሰማን።
አሁን ባለው ሁኔታ ማተሚያ ቤት ገብተናል። እንደሚታወቀው ከሳምንት በፊት ነው ወደ ማተሚያ ቤት የምንገባው። ይህም የሆነበት ባለፉት ሃያ ሦስት ዓመት ውስጥ ማተሚያ ቤት ማግኘት ባለመቻላችን ነው። የወደፊቱን ተፅዕኖ ወደ ፊት እናየዋለን።
አፍሮ ታይምስ ጋዜጣ ለመመስረት ዘጠኝ ወር ብሮድካስት መስሪያቤት ተመላልሰን ነው። አሁን ሥራ በጀመርን በሰባት ወራችን ሊዘጉት ነው።
“የሚሆነው ሁሉ ከምርጫ 2007 ጋር በተያያዘ ነው”
ቶማስ አያሌው የአፍሮታይምስ ጋዜጣ ማኔጅንግ ዳይሬክተር
ጋዜጠኛ ቶማስ አያሌው
ጋዜጠኛ ቶማስ አያሌው



ፍትህ ሚንስትር ያወጣው መግለጫና ክስ ስሰማ ከልብ አዝኛለሁም አፍረያለሁም፤ ያዘንኩት ሁሉንም መፈርጅ ሊያበቃ አለመቻሉ ሲሆን ፤ ያፈርኩት ደግሞ ክስ ቻርጅ ሣይስጥ መግለጫ መውጣቱ ነው፡፡ የሚሆነው ሁሉ ከምርጫ 2007 ጋር በተያያዘ ነው፡፡

source zehabesha 

No comments: