Friday, August 8, 2014

አቶ ሬድዋን ሁሴን በቨርጂኒያ ውርደት ገጠመው፤ ኢትዮጵያውያኑ ልክ ልኩን ነገሩት (ቪዲዮ)

Augest 8/2014
ስንታየሁ ከሚኒሶታ
አቶ ሬድዋን ሁሴን ለሆዱ ያደረ በአራዳ ቋንቋ ‘ችስታ የወያኔ ተላላኪ’ መሆኑን ያሳየው ዛሬ ነው። በአርሊንግተን ቨርጂኒያ። አሜሪካን ውስጥ “ችስታ” ወይም ገንዘብ መቋጠር ከፈለክ የተራረፉ ልብሶችን የምትገዛበት ሱቅ ማርሻልስ ነው። የኬቨን ኪለር፣ ባናና፣ ቦስ፣ ናይኪ፣ አዲዳስ፣ ቶሚ፣ ኤክስፕረስ እና ወዘተ ታዋቂ የልብስና ጫማ አምራች ድርጅቶች በመደብሮቻቸው በሰዎች ልክ (ሳይዝ) የሰሯቸው እቃዎች ወደ ማለቂያ (ፋሽናቸው ሲያልፍ) የሚልኩት ወደ ማርሻልስ ስቶር ነው። ባጭሩ ማርሻልስን በሃገርኛ “ምናለሽ ተራ” ልትሉት ትችላላችሁ።
አዜብ መስፍን አሜሪካ ስትመጣ ጆርጅ ታውን ወርዳ በጣም ውድ የሆኑ ሱቆች ገብታ በ$10 ሺህዎች የሚቆጠሩ ዶላሮችን ታፈሳለች – የሰረቀችው ስላላት። ቴዎድሮስ አድሃኖም ከደሃው ሕዝብ ከሰረቀው ገንዘብ ቀነስ አድርጎ ኒውዮርክ ላይ ጄ ፕሬስ ቡቲክ ገብቶ በሺዎች ዶላሮች ለልብሶቹ አፍሶ ይወጣል። ታይም ስኩዌር ሄዶ ፎቶ ይነሳል። ተላላኪው ሬድዋን ሁሴን ግን ‘ቺፕ’ ብለው አሜሪካውያን በሚጠሩት ማርሻል የተራረፈ ልብስ ገዝቶ ይወጣል:: ዛሬ የሆነውም ያ ነው። ሰውዬው አሜሪካ መጥቶ አዲስ አበባ ላሉት ባለስልጣኖች ከአሜሪካ የገዛሁት ልብስ ብሎ ለማሳየት ከአሜሪካው ምናለሽ ተራ ሱቅ ልብስ ሊገዛ ገብቶ ተዋርዶ ተመለሰ። ኢትዮጵያውያኑ ተጋፈጡት። ሌባ መሆኑን፤ ገዳይና የገዳይ አገልጋይ መሆኑንም የፊቱ ቆዳ የሳሞራ የኑስን ልብስ እስኪመስል ድረስ ነገሩት።
እንደለመደ አፉን አይከፍት ነገር ያለው አሜሪካ ሆነበት፤ እንዳይደነፋ ኢቲቪና መቀሱ የሉም። ውርደቱን ከኤክስፕረስ በታላቅ ቅናሽ የገዛውን ሰማያዊ ልብስ እንደለበሰ ተከናንቦ ተመለሰ። ወይ ሬድዋን፤ አዜብ ጆርጅ ታውን፣ ቴዎድሮስ ጄፕሬስ ሲገበያዩ አንተ ቺስታና ሆድ አደር ስለሆንክ በማርሻል ውርደትህን አከናነቡህ አይደል? ገና ምን አይተህ? ኢትዮጵያውያኑ የሳሞራ የኑስን ልብስ እንዲመስል ያደረጉልህ ቆዳህ ገና ወደ የት እንደሚሄድ አብረን እናየዋለን።
ሬድዋንን የተጋፈጡትን ብርቱ ኢትዮጵያውያንን እያደነቁ፤ የወያኔ ተላላኪዎችን የማወረዱ ሥራ እንዲቀጥል አደራ እላለሁ። ቪድዮውን እነሆ።



No comments: