June 5/2014
አንድነት ፓርቲ በመጪው ዕሁድ ሰኔ 1 ቀን 2006 በደብረማርቆስ፣ በአዳማ/ናዝሬት እና በቁጫ/ሰላም በር ከተማ የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት በሚል መሪ ቃል ለሚያካሂደው የተቃውሞ ሰልፍ፤ የቅስቀሳ ስራውን የሚያስተባብሩ ሶስት ቡድኖች ከትላንት ጀምሮ ከዋናው ጽ/ቤት መንቀሳቀስ ጀምረዋል፡፡ ዛሬ በቁጫ/ሰላም በር ከተማ የሚደረገውን ቅስቀሳ የሚያስተባብረው ቡድን ወደ ስፍራው አቅንቷል፡፡ በደብረ ማርቆስና በአዳማ የተጠናከረ ቅስቀሳ ከተሰራ በኋላ የፖሊስ የተሟላ የዕውቅና ማስረጃ የያዙት 10 የአንድነትን ደብረ ማርቆስ ላይ እንሁም 9 የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላትን ደግሞ አዳማላይ አስሯል፤ በተጨማሪም የአንድነት ፓርቲ የአዳማ ከተማ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆነው አቶ ተስፋዬ ዋቅቶላን ከሌሎች አመራሮችና አባላት ተነጥሎ እንደታሰረም ለወቅ ተችሏል፡፡![10390527_646975422054062_5390340408407620827_n](https://lh3.googleusercontent.com/blogger_img_proxy/AEn0k_ucAv0DnLe-P8viSYHbnLq-gjegN2OmeA6aOp7eJ-M3Tkhzr1GvVJzfxE7DTShPPR7jSY1B0cAHI6Qp1diWii7TALozHOFswHL0sHQfyZHI4aB2PRViude3DZuzI1WcwqlMtz2eS0TkMpK9F2jvWKsLZ4gLsuS_5s8wWiPSknzB0vUF6dTLApXF45JW9VKZw0hTPGhWsSRNliHPkA=s0-d)
No comments:
Post a Comment