Monday, June 23, 2014

የአምባገነኖችና ዴሞክራሲ ናፋቂዎች ግብግብ በአዋሳ – ዳንኤል ተፈራ

June23/2014
አዋሳ ሆይ እስከመቼ የዳንስ ከተማ ብቻ እንድትሆኝ ይፈረድብሻል? የፖለቲካ ከተማም ሁኝ እንጅ!!!የህዝቡ የለውጥ ፍላጎት ገፍቶ በወጣ ቁጥር የአምባገነኖች መደናበር ያይላል፡፡ ሲደናበሩም ህግ ይጥሳሉ፣ ህዝብ ያሰቃያሉ፣ ሀገር ይበድላሉ፡፡ ግን እድሜ ልክ ዕየተጨቆኑ መኖር አይቻልም፡፡ ‹‹ተቀምጦ ከመኖር ቆሞ መሞት ይሻላል›› እንዲሉ፡፡ ቆሜ መሞት ይሻለኛል የሚሉ ዴሞክራሲ ናፋቂዎች እየበረከቱ ነው፤ እምቢ ከፈለግህ ይሄው እሰረኝ! የሚሉ ትንታግ ወጣቶች እየተፈጠሩ ነው፡፡
እንደዚህ እንድል ምክንያት የሆነኝ ‹በደቡብ ክልል› አዋሳ ከተማ አንድነት ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቶ ነበር፡፡ ህጉንም ጠብቆ ለሚመለከታቸው አካላት አሳውቆም ነበር፡፡ ትናንት ይካሄድ ለነበረው የተቃውሞ ሰልፍም አዋሳ ካለው መዋቅር ጋር ተቀላቅለው ቅስቀሳ የሚያካሂዱ ትንታግ ወጣቶች ከአዲስ አበባ አዋሳ ገብተውም ነበር፡፡
ነገር ግን የአቶ ኃይለማርያምን በድጋፍ ወደ ስልጣን መምጣት ተከትሎ በተለይ በደቡብ የገዥነት መጥፎ ስሜት የተጠናወታቸው የታች ባለስልጣናት ህግ በአደባባይ እየደፈጠጡ ነው፡፡ ስለዚህ በቅስቀሳ ላይ የነበሩትን አባላትና አመራሮች አሰሩ፡፡ ዴሞክራት ወጣቶች ግን በእስሩ አልተበገሩም ‹‹ህጉን ጠብቀን አሳወቅን፣ የእውቅናውን ደብዳቤ መስጠት ይህን ሊሰራ የተቀመጠው አካል ድርሻ ነው፡፡ እውቅና ወረቀቱን የሚሰጠው አካል ስራውን ስላልሰራ እኛ ስራ ማቆም የለብንም፡፡›› በማለት ስራቸውን እንደሚቀጥሉ አሳውቀዋቸዋል፡፡ ይህ የሆነው ሐሙስ ነበር፡፡ አሳሪዎቹ ያለምክንያት ማሰራቸው ሲያስጨንቃቸው ማታውኑ ‹‹ነገ እንዳትቀሰቅሱ፣ ከቀሰቀሳችሁ እናስራችኋለን›› ብለው ይለቋቸዋል፡፡
ትንታጎቹ የዴሞክራሲ ናፋቂዎች ግን ህገ ወጡን ትእዛዝ አልተቀበሉም፡፡ ህገወጡን ትእዛዝ ከመቀበል መታሰር እንደሚሻል ወሰኑ፡፡ አርብ ጠኋትም ወደ ቅስቀሳቸው ገቡ፡፡ አሳሪዎችም ካቴናቸውን ይዘው መጡና አሰሯቸው፡፡ በአጠቃላይ በአዋሳ የሚገኙ አመራሮችንና አባላትን ከየቦታው ለቃቅመው አሰሯቸው፡፡ ሰልፉም በዴሞክራሲ ደፍጣጮች ጉልበት ለጊዜው ተስተጓጎለ፡፡
10488127_656125691139035_1357107079390830511_nግን ግን ‹‹መብቴን አሳልፌ ከምሰጥ መታሰርን እመርጣለሁ!!!›› የሚለውን የዚህ ትውልድ ቁርጠኝነት እንዴት ማሸነፍ ይቻላቸዋል???
10407259_656125577805713_222556347364704833_n
10269554_656125667805704_1964284731181619666_n
10488248_656125737805697_5478378998562656693_n
10403063_655210891230515_1638818640015330651_n

No comments: