Saturday, January 4, 2014

አንድነት 6 5% በወጣቶች የተሞላዉ የአንድነት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ (ካቢኔ)

Januray4/2014
በአንድነት ፓርቲ ምተዳደሪያ ደንብ መሰረት የድርጅቱን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ(ወይንም ካቢኔ) የሚመርጡት የድርጅቱ ሊቀመንበር ናቸው። ሊቀመነንበሩ በጠቅላላ ጉባኤ የሚመረጡ ሲሆን፣ የካቢኔ አባላትን ደግሞ ብሄራዊ ምክር ቤቱ  ያጸድቃል። የብሄራዊ ምክር ቤቱ እሽታ ያላገኘ የካቢኔ አባል ተቀባይነት አይኖረዉም።
Andinet Party Leadership
በዚህ መሰረት አዲሱ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር፣ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራዉ፣  አሥራ ሁለት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን መርጠዋል። «የካቢኔ አባላቱን ከመምረጤ በፊት፣ አባላቱ አስተያየትና ጥቆማ እንዲሰጡኝ በሩን ክፍት በማድረግ የብዙዎችን አስተያየት ተቀብያለሁ፡፡ ሌላው መስፈርቱ የትምህርት ዝግጅት፣የፖለቲካ ልምድና ተባብሮ የመስራት ባህል ለመመልከት ሞክሪያለሁ፡፡በዚሁ መሰረትም የሚከተሉትን ሰዎች የካቢኔ አባላት እንዲሆኑ ወስኛለሁ» ነበር ያሉት እንጂነር ግዛቸው ሽፈራዉ።  ከካቢኔው አባላት መካከል ከ65 በመቶ በላይ በወጣቶች የተገነባ ነው፡፡ስድስት የማስተርስ አራት ባችለር ሁለት ዲፕሎማ ያላቸው መሆናቸውን ፕሬዘዳንቱ ገልጸዋል፡፡
1) አቶ ተክሌ በቀለ ——- ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት
2) አቶ በላይ ፈቃዱ ——– ምክትል ፕሬዘዳንት
3) አቶ ስዩም መንገሻ ——– ዋና ጸሀፊ
4) አቶ ዳንኤል ተፈራ ——– የድርጅት ጉዳይ ሀላፊ
5)አቶ ሃብታሙ አያሌው ——- የህዝብ ግኑኝነት ሀላፊ
6)አቶ ዘለቀ ረዲ ——— የውጪ ጉዳይ ሀላፊ
7) አቶ አስቻለው ከተማ ——- የፋይናንስ ጉዳይ ሃላፊ
8)አቶ ሰለሞን ስዮም ——– የፖለቲካ ጉዳይ ሃላፊ
9) አቶ ዳዊት አስራደ ——– የኢኮኖሚ ጉዳይ ሃላፊ
10)አቶ አለነ ማህጸንቱ ——- የማህበራዊ ጉዳይ ሃላፊ
11) ወ/ሮ የትናየት ቱጂ ——- የህግና ሰብአዊ መብት ጉዳይ ሃላፊ
12) አቶ ትእግስቱ አወሉ ——- ( የአዲስ አበባ ምክር ቤት ሃላፊ በመሆናቸው በቀጥታ የካቢኔ አባል ሆነዋል)
አቶ ተክሌ በቀለ ድርጅቱን ለመመራት ከኢንጂነር ግዛቸው ጋር ሲፎካከሩ ጠንካራ የአንድነት አባል ሲሆኑ፣ አቶ በላይ ፈቃዱ ደግሞ የሚሊየነም ድምጽቾ ለነጻነት ግብረ ኃይል እንዲሁም የፍኖት ጋዜጣ ኤዲቶሪአይል ቦርድ ሲመሩ የነበሩ ጠንካራ የደርጅቱ አባል ናቸው።
አቶ ሃብታሙ አያሌው በቅርቡ በኢቲቪ በጸረ-ሽብርተኝነት ሕጉ ዙሪያ በተደረገዉ ክርክር የአንድነት ፓርቲ ወክለው የቀረቡ ወጣት የአንድነት አባል ናቸው። የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ የነበሩት አቶ አቶ ዳንኤል ተፈራ፣ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ ሆነዋል።

No comments: