Tuesday, March 19, 2013

የኢትዮጵያውያን ጩኸት ከመካከለኛው ምስራቅ---በሳኡዲ የመን ድንበር የታሰሩ እስረኞች ለመልቀቅ ገንዘብ እየተጠየቁ ነው::


በሳኡድ ፖሊሶችዛፍ ላይ  የታሰረው ኢትዮጵያዊ 
በሺዎች የሚቆጠሩ በሳኡዲ የመን እስር ቤት ያሉ ስደተኞች አስፈላጊውን ክፍያ እየከፈሉ እንደሚለቀቁ የየመን የደህንነት ባለስልጣን መሃመድ ነጃድ አስታወቁ::

ሁነታዎችን አደገኛ ያደረገው ባለፈው የካቲት ወር ላይ ኢትዮጵያውያን ለሃገራቸው አደገኛ እና ህገወጥ አስጊ መሆናቸውን የሳኡዲ ሚዲያዎች (  http://www.youtube.com/watch?v=DSS4bAVP-fA  )الكنبه إذا عزمك أثيوبي تروح له ؟ / Couch if your determination Ethiopian his imagination?/ የተላለፈውን ዘገባ ተከትሎ ነው:: ይህን ዘገባ የሰሙ የሳኡዲ እና የየመን ዜጎች በድንበሩ አከባቢ እና በሳኡዲ አረቢያ ውስጥ ህገወጥ ናቸው ያሉዋቸውን ሰዎች እየያዙ ያስረክባሉ ቢባልም እውነታው ግን ከኢትዮጵያውያን ገንዘብ እንዲያመጡ ያስገድዷቸዋል::

በሳ ኡዲ  አሰሪዎቹ የተቃጠለው ኢትዮጵያዊ 
በህገወጥ ደላሎች የተደፈሩ ሴቶች 
በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የኢኮኖሚ ድቀት እና የፖለቲካ አምባገነንነት ሸሽተው ወደየሰዉ አገር የሚሰደዱት ወገኖች
በወጣትነታቸው ሰርተው ራሳቸውን እና ቤተስቦቻቸውን ለመርዳት እንኳን አልታደሉም::ከተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ድርጅት( http://www.un.org/apps/news/story.asp?NewsID=43928&Cr=yemen&Cr1=refugee#.UUiOcDcj8wq ) ባወጣው ዘገባ 84.000 ኢትዮጵያውያን የኤደንን ሰርጥ አቋርጠው በአስፈሪው የውሃ ማዕበል አልፈው ወደ መካከለኛው ምስራቅ ያቋርጣሉ::

አብዛኛው አስቸጋሪውን የባህር ጉዞ የጨረሰው በቀጥታ ወደ የመን ሳኡዲ ድንበር ይሄድ እና በህገወጥ ደላሎች እና ድንበር አሻጋሪዎች ወደ ሳኡዲ ለመግባት ሲሞክር በወሮበሎች በዘራፊዎች በአጭበርባሪዎች ገንዘቡን ይበላል ተይዞ ለፖሊስ ያስረክቡታል ፖሊስም ድጋሚ ገንዘቡን ይነጥቀዋል ::
በቅርብ ጊዜ የወጣ የUNHCR ሪፖርት ( http://www.middle-east-online.com/english/?id=51172 ) እንደሚያመለክተው የየመን እና የሱዲ የድንበር ላይ ባለስልጣናት ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ ኢትዮጵያውያንን አስገድደው ይደፍራሉ:ገንዘባቸውን በጉልበት ይነጥቃሉ ይላል::እንዲሁም ከቤተሰቦቻቸው ገንዘብ ይጠይቃሉ ያሌለውን ገድለው አካሉን በጥቁር ገበያ ይሸጡታል:: http://www.youtube.com/watch?v=2zTA4U0W3DI&feature=player_embedded

በሳዑድ ፖሊሶች የተያዙ ኢትዮጵያውያን በመኪና ታስረው በየተራ ሲጎተቱ 
በየመን አደን ባህር ላይ የተገኘች ኢትዮጵያዊ ከነልጇ









No comments: