Tuesday, March 26, 2013

የመድኀኔዐለም መሰናዶ ት/ቤት ተማሪዎች ተቃውሞቸውን አሰሙ!!!

by
Image
ዛሬ የመድኀኔዐለም መሰናዶ ት/ቤት ተማሪዎች ከባድ ተቃውሞ አሰሙ:: በዚህ ተቃውሞ ላይ ከት/ቤቱ ተማሪዎች ከግማሽ ያላነሱ ተሳትፈዋል:: የዚህ ተቃውሞ ምክንያት የሆነው በትላንትናው እለት በተማሪዎች የመግቢያ ሰዐት ላይ ማሻሻያ ከተደረገ ቡሀላ ነው:: ማለትም ከዚህ በፊት ተማሪዎቹ የት/ቤቱ ቅጥር ጊቢ ውስጥ የሚገኙት ከ2:40-2:50 ዛሬ ግን ባልተለመደ መልኩ የት/ቤቱ አመራሮች 2:30 አካባቢ ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቹ የሚገቡበትን በር በመዝጋት እንዳይገቡ ከልክለዋል:: ተማሩዎቹም ከዚህ በፊት ችግራቸውን የተናገሩ ቢሆኑም ድምፃቸውን የሚሰማቸው አተዋል:: ለማርፈዳቸው እንደ ትልቅ ምክንያት ካቀረቡት ውስጥ ፒያሳ ከሚገኘው ከማስታወቂያ ሚኒስቴር ጀምሮ እስከ ዊንጌት አካባቢ እየተሰራ ባለው መንገድ ምክንያትና ጊዮርጊስ ቤ/ክ አካባቢ በሚሰራው የባቡር ትራንስፖርት ግንባታ የተነሳ በዚያ አካባቢ ጉዞአቸውን የሚያደርጉ መኪኖች መስመራቸውን በማስታወቂያ ሚኒስትር በኩል ስላደረጉ የትራፊክ ፍሰቱ እጅግ አዳጋች እንደሆነ ተናጋረው ነበር:: ዛሬ ተማሪዎቹ ወደ ክፍል እንዲገቡ በሰላም ጠይቀው ቢሆንም የሚሰማቸው በማጣታቸው ከፍተኛ ጩኸቶችን እና የት/ቤቱን ር/ምህር የሚነቅፉ መፈክሮችን አሰምተዋል:: ከነዚህ መካከል
ሺበሺ ሌባ ነው!
ሺበሺ ጋዳፊነው!
ሺበሺ ይታሰር!
የሚሉት በሰፊው ተስተጋበተዋል:: ከአንዳንድ ተማሪዎች እንዳጣራሁት ከሆነ ይህ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ነጭ ጋዎን ያደረገው አቶ ሺበሺ ብሩ የሚባለው ር/መምህር በት/ቤቱ ተማሪዎች እጅግ የሚወገዝ መሆኑን ነግረውኛል:: ለዚህ ምክንያት ተማሪዎችን እንደ ሚያመናጨቅና ያልተገቡ ቃላትን እንደሚጠቀም ነግረውኛል:: በሌላም በኩል ይህ ሰው ባለፉት ሳምንታት አንድ ተማሪን አግባብ ያልሆነ ምት መቶት የተማሪው ጆሮ በእጀጉ እንደተጎዳ ታውቆአል:: ፍርድ ቤትም ቀርቦ አንደ ነበር ለማወቅ ተቸልዋል::

No comments: