Friday, March 29, 2013

ኢትዮጵያን ከወያኔ ስርዓት የማላቀቂያ ጊዜው አሁን ነው (ገዛኸኝ አበበ ኖርዌይ)

  march 29/2013 

ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ

ወያኔ ኢሕአዴግ ኢትዮጵያን በሀይል መግዛት ሕዝብን በአፈናና በእንግልት ማሰቃየት ከጀመረ ሀያ ሁለተኛ ዓመቱን ለማክበር ባለበት በዚይ ጊዜ በኢትዮጵያ ላይ ብዙ ለውጦች እንዳመጣ እና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ወደ ተሻለ የእድገት ደረጀ እያመራ እንዳለ የሕዝቡም የኖሩ አቀጣጫ እንደተለወጠ አፉን ሞልቶ ሲናገር እንስመዋለን ወያኔ ኢሕአዴግ የፖለቲካ ስልጣኑን ለማስረዘመ ይህንን ይበል እንጂ ሀቁ ግን ይህ አይደለም :: በኢትዮጵያ ላይ የሚደረጉ አለም ዓቀፍ ጥናቶች እና ሐሀዞች እንደሚያሳዩት ወያኔ በስልጣን በቆየባቸው በእነዚህ ሁለት አስር ዓመታቶች በአገሪቷ ላይ አስከፊ ድህነት እንደሰፈነ ፣ የስራ አጥ ቁጥር እንዳሻቀበ እና ፣ ሰበዓዊ እና ፣ ዲሞክራሳዊ መብቶች ክብር አልባ ሆነው ፣ የገአሪቷ ዜጕች የኖሮ ደረጃ ከቀነ ወደ ቀን እንዳሽቆለቆለ ነው::

      ወያኔ ኢሕአዴግ በሀገሪቷ ላይ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ እንደል ይለፍልፍ እንጂ አሁንም እየታየ ያለው ሀቁ ግን እንደሚያሳየው በአገሪቷ ላይ የአንድ ብሔር  የበላይነት ብቻ የሚነጸባረቀበት መሪዎች የፖለቲካ ስልጣንን ለግል ጥቅም ማካበቻ የሚጠቀሙበት ዘረኛ እና ጨቆኝ ስርዓት የነገሰባት ሀገር አንዷ ኢትዮጵያ እንደሆነች ነው :: ይህንንም ብልሹ እና አስከፊ ስርዓት የሚቃወሙ እና የሚተቹ ሰዎች በማን አለብኝነት በወያኔ የግፍ በትር በየእስር ቤቱ በስቃይ መከራ እየተንገላቱ እንደሚገኙ እና አብዛኛውም የአገሪቱ ሕዝቦች የተበላሸው የወያኔ ስርዓት በፈጠረው የኑሮም ሆነ የፖለቲካ ጫና በመሸሽ አገራቸውን ትተው ለስደት እና ለመከራ ሲዳረጉ አብዛኞቹም ያሰቡበት ሳይደርሱ ሕይወታቸው እንደዋዛ አልፉል :: መረጃዎች እንደሚያመለክቱት የኢትዮጵያ ሕዝብ ከቀን ወደ ቀን በብዛት አገሪቷን እየተወ ባገኘው አጋጣሚ ወደተለያዩ አገሮች ከሚሰደድበት አገር ተርታ እንደምትመደብ እና ወያኔ አገሪቱን ወደተሻለ የእድገት ደረጃ እየመራ እንዳለ ይናገር እንንጂ አገሪቷ ግን ከታች ካሉ የደሃ አገሮች ግንባር ቀደም እንደሆነች እና አገሪቷ ወደ መጥፎ አቅጣጫ እያመራች እንዳለ ነው የሚያመለክተው::

         የዜጎች የመብት ረገጣ ፣ አፈና ፣ስቃይ ከመቼውም በላቀ ጊዜ ላይ ይገኛል:: ሀገሪቷም በመጥፎ ሁኔታ ውስጥ ናት:: ለዚህም ነው የኢትዮጵያ ፊዲራላዊ አነድነት መድረክ መጋቢት 17 ቀን 2005 የሀገሪቱን ጊዚያዊ ሁኔታ አስመልከቷ በሰጠው ጋዚጣዊ መግለጫ ላይ አገሪቱ መስቀለኛ መንገድ ላይ ትገኛለች ያለው::

   አሁን ላይ እንደሚታየው የአገሪቷ ተጨባጭ ሁኔታ በጣም አስከፊ እና አሳሳሳቢ ሁኔታ ላይ ነው :: ለተቀዋሚ የፖለቲካ ድርጅቷች ደግሞ ጥሩ መነሳሳት የሚሆን አጋጣሚ እና በወያኔ መንግስት ላይ ስር ነቀል ርምጃ ለመውሰድ የሚነሳሱበት ወቅት ነው :: በርግጥ በአሁኑ ሰዓት በወያኔ ኢሕአዴግ መካከል አይለኛ የሆነ የእርስ በእርስ ሽኩቻ እና እርስ በእርስ የመናናቅ ፣ ያለመከባባር እና የመከፋፈል ትርምስ እንዳለ ለከፍተኛ ባለስልጣን ሳይቀር በድርጅቶ ውስጥ እየሆነ ያለው ሁኔታ አሳሳቤ እንደሆነባቸው ምንጮች ገልጸዋል:: ይህ ሁሉ የሚያሳየው የወያኔ ኢሕአዴግ የስልጣን ዘመን እየተፍረከረከ መምጣቱን ነው :: በአሁኑ ሰዓት የወያኔ ካድሪዎች ተደናግጠዋል ምን እየሰሩ እንዳለ እንኮን አንደማያቁ ነው ::  ሰሞኑን በባሕር ዳር በተካኤደው ዘጠነኛው የኢሕአዴግ ጉባኤ ላይ ያየነው ይህንኑ ነው::


     የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር ባለቤት አዜብ መስፍን ባለቤታቸው ያገኘው ሰለነበረው የወር ደሞዝ ስትናገር በጣም አሳፋሪ እና ሴትየዋንም ለትዝብት የሚዳርጋት ንግግር ነበር የተናገረቸው :: አንዳንድ የፖለቲካ ሰዎች እንደሚሉት ሴትየዋ ይህን ንግግር ልትናገር የቻለችበት ምክንያት ወደ ስልጣን እየመጡ ያሉትን አዳዲስ የኢሕአዴግ ሰዎችን ሸንቆጥ ለማድረግ የተጠቀሙበት ፕሮፑጋንዳ እንደሆነ ይናገራሉ:: በርግጥ ሲትዮዋ  ይህን ስትናገር በጉባኤው ላይ የተሰበሰብትም ሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ ንግግሮን ምን ያክል ውሸት እንደሆነ እንደሚያቁው ታውቀዋለች ምክንያቱም የኢትዮጵያ ሕዝብ ከመረጃ ያልራቀ ሕዝብ ነውና:: ነግር ግን የአዜብ መስፍን ንግግር ኢሕአዴግ ባለስልጣኖች ምን ያክል በስጋት እና በድንጋጤ ውስጥ እየኖሩ እንዳለ አመላካች ነው :: በአሁኑ ሰዓት በማን አለብኝነት በኢሕአዴግ ውስጥ ትልቁን የፖለቲካ ሚና እየተጫወተ ያለው ህወሓት ሳይቀር ከወትሮው ጊዜ በተለየ መልኩ በታላቅ ክፍፍል እና ሽኩቻ ውስጥ እንደሚገኝ የውስጥ ምንጮች እየጠቀሱ ባሉበት በእዚህ ወቅት የተጠናከረ እና የተደራጀ የፖለቲካ እና የሰው ኃይል ቢኖር ኢትዮጵያን ከወያኔ ስርዓት የማላቀቂያ ጊዜው አሁን እንደሆነ በብዙዎች ዘንድ የተመነበት ሀቅ ነው ለዚህም ሁሉም የወያኔ ተቃዋሜ ድርጅቶች በአንድነት መነሳት ያለባቸው :: ሕዝቡም ለሁለት አስር ዓመታት በወያኔ የግፍ እና የጭቆና ስርዓት ውስጥ የኖረበት ጊዜ በቃኝ በማለት ለነጻነቱ እና ለዲሞክራሳዊ መብቱ መከበር ሲለ በወያኔ ስርዓት ላይ የተቃውሞ ድምጹን ማሰማት ይጠበቅበታል::

በቃ !!!



   ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ





  

No comments: