Friday, March 15, 2013

ወሓት ስብሰባ ተጠናቀቀ!! ‘ፀላእትና ክንከራታትሞም ኢና!’ ብለዋል

(ኣብርሃ ደስታ ከመቐለ) ሦስት ቀናት የፈጀው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ኣባላት ስብሰባ ትናንት ተጠናቋል። ለጉባኤው የሚሆን ኣጀንዳ ለመለየትና ልዩነታቸው ለማጥበብ ሲነታረኩ ቆይተው ቀጣዩ 11ኛ የህወሓት ድርጅታዊ ጉባኤ በሰላም ለማጠናቀቅ የተስማሙ ይመስላሉ።የስብሰባው ተስታፊዎች በሁለት ተከፍለው ዘለፋና የጠብ መንፈስ የተሞላበት ጭቅጭቅ ከተካሄደ በኋላ ሌላ ሦስተኛ ቡድን ተፈጥሮ “ህወሓትን እናስቀደም፣ ልዩነታችን ወደ ጎን ትተን የጋራ ጠላቶቻችንን እንታገል፣ ሁለታቹ (ቡድኖቹ) የህዝብ ድጋፍ የላችሁም፤ ስለዚ በሁለት ከተከፈልን ህወሓት ህልውናው ያበቃል።” ሲል ተማፅነዋል።በዶክተር ቴድሮስ ኣድሓኖም የተመራ የሽምግልና ጥረት ታድያ ሁለቱም ቡድኖች ልዩነታቸው ኣጥብበው ኣብረው በጉባኤው እንዲሳተፉና በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸው እንዲተባበሩ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።ልዩነታቸው ግን የከረረ ጠብ እንደወለደና እስካሁን ‘ የእግዚሄር ሰላምታ’ እንኳ እንደማይለዋወጡ ተነግረዋል። ኣሁን ባይለያዩም የመከፋፈሉ ኣደጋ ግን እንዳለ ነው። የቸገራቸው ነገር ኣንዳቸው ሌላኛው ቡድን ቢያሸንፍ እንኳ ለብቻው ህወሓትን ለማስቀጠል የሚያስችል የህዝብና ካድሬ ድጋፍ እንደማያገኝ ተረድተዋል።የሚቀጥለው የህወሓት 11 ኛ ድርጅታዊ (ዉድባዊ) ጉባኤ “ጉባኤ መለስ” (የመለስ ጉባኤ) ተብሎ ተሰይመዋል። መለስ የሁለቱም (የሁሉም) ቡድኖች የጋራ ነጥባቸው ነው።ከጉባኤው በኋላ “ጠላቶች” ያሉዋቸውን ኣካላት እንደሚመቱ (እንደሚጨፈልቁ) ዝተዋል። ‘ ፀላእትና ክንከራታትሞም ኢና!’ የሚል መግለጫ ኣውጥተዋል። ወይ መዓልቲ

No comments: