Friday, January 3, 2014

ህወሃት ኢህአዴግ ስራ-ኣጥ ለሆኑ ወጣቶች ስልጠና ለመውሰድ ተመዝገቡ ብሎ በማታለል ወታደራዊ መሰልጠኛ እንዳስገባቸው ታወቀ

January 3, 2o14

በመረጃው መሰረት በአማራ ክልል ጎንድር ከተማ ከተለያዩ ዩንቨርስቲዎችና ኮሌጆች በድግሪና በዲፕሎማ የተመረቁ እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀው ነጥብ ያልመጣላቸው ወጣቶች ሥር-ዓጥ ሁነው የግል ሂወታቸውን ለመምራት ላይና ታች ሢሉ የታዘቡ የከተማዋ አስተዳዳሪውች። በስርዓቱ ላይ ምንም አይነት እምነት እንደሌላቸው በአንፃሩ የሚረዳና የሚደግፋቸዉ አካል ካገኙ በስርዓቱ ላይ እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ እንዳማይሉ ስለተረዱ፤ ወጣቶችን ለመበተን ብለው በመንግስት የሚሰጣችሁ ሞያዊ ስልጠና እንደ አለ ኣስመስለው በማታለል ብር ሽለቆ ወደ ሚገኘው ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምብ እንደወሰድዋቸው ታወቀ::

ይህ በእንዲህ እንዳለ እነዚህ የኢህአዴግ ጸረህዝብ ካድሬዋችና አስተዳድሪች ለወጣቱ እንደማታለያ የሚጠቀሙበት ዘዴ፤ ዘመናዊ በሆነ የሞያ ማሰልጠኛ ማለት የዲዛይን ማውጣት ስራ፤ የብረታብረትና የእንጨት ጥርበት፤ የሾፌርነትና የመካኒክነት ስልጠና ስላለ ሙሉ በሙሉ በቂ የሆነ ስልጠና ወስዳችሁ በማነኛዉም አካባቢ ስራ ተቀጥራችሁ ሂወታችሁን መምራት የሚያስችላችሁን አቅም እንድትጨብጡ መንግስት በቂ የሆነ በጀት መድብዋል ብለው እንደተናገርዋቸው ለማወቅ ተችልዋል::

ይሁን እንጂ በመኪና ጭነው ወደ ብርሽለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምብ ተወስደው ወትሃደራዊ ስልጠና በመጀመራቸው፤ ወጣቶቹ በበኩላቸው የመጣ ይምጣ በለው፤ ለምን በሂወታችን ላይ ትጫወታላችሁ የሚል ጥያቄ እንዳቀረቡላቸውና ለስልጠናው ተቃውመው ሲጠፉ ለተያዙ ወጣቶች እንዳይናገሩ ፈርተው ወደ ስራ ሲያስገብዋቸው ለቀሩት አሰልጥነው በጎጃም አካባቢ ስብስበዋቸው እንደሚገኙ የተገኘው መረጃ ኣስረድተዋል::

Source : ዴ.ም.ህ.ት

No comments: