Thursday, November 21, 2013

ኢህአዴግ ስለምን ይጮኻል? (ተመስገን ደሳለኝ)

November 21/2013

በረዥሙ የኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ታሪክ፣ በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳ አንድም ድርሳን ፈልጎ ማግኘት የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ሁሉም መንግስታት የተወገዱት በአመፅ አሊያም በተፈጥሮ ሞት ነውና፡፡ በ1983 ዓ.ም ወርሃ ግንቦት በጠብ-መንጃ ኃይል ሥልጣን የተቆናጠጠው ኢህአዴግ- መራሹ መንግስትም ቢሆን፣ በቀድሞዎቹ ገዥዎች ‹የብረት ጫማ› ውስጥ ተከልሎና ተደላድሎ ዕለተ-ስንብቱን በመጠባበቅ ላይ ያለ ይመስለኛል፡፡ ዕለተ-ስንብቱ መቃረቡን የሚጠቁመው ደግሞ ከቅርብ በረዥሙ የኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ታሪክ፣ በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳ በረዥሙ የኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ታሪክ፣ በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳበረዥሙ የኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ታሪክ፣ በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳ አንድም ድርሳን ፈልጎ ማግኘት የሚቻል አይመስለኝም፡፡ 

ሁሉም መንግስታት የተወገዱት በአመፅ አሊያም

በተፈጥሮ ሞት ነውና፡፡ በ1983 ዓ.ም ወርሃ ግንቦት በጠብ-መንጃ ኃይል ሥልጣን የተቆናጠጠው ኢህአዴግ-
መራሹ መንግስትም ቢሆን፣ በቀድሞዎቹ ገዥዎች ‹የብረት ጫማ› ውስጥ ተከልሎና ተደላድሎ ዕለተ-ስንብቱን
በመጠባበቅ ላይ ያለ ይመስለኛል፡፡ ዕለተ-ስንብቱ መቃረቡን የሚጠቁመው ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ልክ
እንደ ደርግ የመጨረሻዎቹ ወራት ሁሉ፣ ግንባሩና አጋር ፓርቲዎቹ ለየት ባለ መልኩ በራሳቸውና
በሹማምንቶቻቸው ላይ በአደባባይ የተቃውሞ ድምፅ ማሰማት መጀመራቸው ነው፡፡ የዚህ ፅሁፍ ተጠየቅም
ይህ ነውና ተጨባጭ እውነታውን ለማብራራት በቂ የሆኑ አስረጂዎችን በአዲስ መስመር በዝርዝር ለመመልከት እሞክራለሁ፡፡ 

ስረጅ አንድ
በ2005 ዓ.ም መጨረሻ ላይ የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ዓመታዊ ሪፖርቱን ለሕዝብ ተወካዮች ባቀረበበት ወቅት ከአገዛዙ የተለየ
ድምፅ የተሰማው እንደ ወትሮው ሁሉ፣ በም/ቤቱ ተቃዋሚ ፓርቲን ከወከለው ‹አንድ ለእናቱ› አቶ ግርማ ሰይፉ ብቻ አይደለም፤
ኢህአዴግ በአምሳሉ ከፈጠራቸው አጋር ፓርቲዎችም ጭምር እንጂ፡፡
በዕለቱ ሚንስትሩ ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም በመንግስት በመገንባት ላይ ያለውን የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካን አስመልክቶ ‹አክራሪ›
ካላቸው መነኮሳትና ‹ጥቂት› መዕምናን ‹ግርግር የመፍጠር ሙከራ› ባለፈ የተከሰተ የጎላ ችግር አለመኖሩን በሪፖርቱ መጥቀሱን ተከትሎ
የአፋር ክልል ተወካዩ በአጋርነት ያነበረውን ስርዓት እንዲህ ሲል ነበር የተቸው፡-
‹‹ለፋብሪካው ግንባታ ተብሎ ከአካባቢው የተፈናቀሉ ነዋሪዎች እንዲሰፍሩ የተደረገበት ቦታ ውሃና መብራት ያሌለው ነው፤ ይህ ለምን
ሆነ? ብለን ስንጠይቅ ‹ድሮም የነበሩበት ቦታ መብራትና ውሃ የለውም› በማለት ይመልሱልናል፡፡ በአጠቃላይ በአፋርና አካባቢው
በሪፖርቱ ያልተካተቱ ብዙ ችግሮች አሉ፡፡››
የሶማሌ ክልል ተወካይም በበኩሉ በዚሁ ዕለት የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ‹የሰብዓዊ መብት አያያዝ›ን በተመለከተ አድበስብሶ ማለፉን
የተቃወመው በሚከተለው አኳኋን ነበር፡-
‹‹በእኛ አካባቢ የሰብዓዊ መብት አይከበርም፤ ሰዎች ይገደላሉ፤ ይታሰራሉ፤ ይደበደባሉ፡፡›› (በርግጥ በመልከዓ ምድር ለአካባቢው
ከማንም በላይ የሚቀርበው የሀረሪው ተወካይ ብዙውን ጊዜ በምክር ቤቱ ስለማይገኝ በዕለቱ በቀረበው ሪፖርት ላይ ቅሬታ ይኑረው ድጋፍ
ማወቅ አልተቻለም)
አስረጅ ሁለት
ጥቅምት 22 ቀን 2006 ዓ.ም የኢትዮጵያ የሰላምና ልማት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር አቦይ ስብሃት ነጋ፣ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት
ለውጭ፣ መከላከያና ደህንነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የዓመቱን በጀት ለማፀደቅ ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
መ/ቤት ጋር ተግባብተው መስራት አለመቻላቸውን በግልፅ ተናግረዋል፡፡ ኢንስቲትዩቱ የተመሰረተበት አቢይ ዓላማ ‹‹የውጭ ጉዳይ
ፖሊሲ በሚያስገኘው ውጤት ዙሪያ ጥልቅ ጥናት ለማካሄድ›› መሆኑ ቢታወቅም፣ ውጭ ጉዳይ ‹‹ይህንን አጥኑልን›› ብሎም ሆነ አቅጣጫ
አሳይቶ እንደማያውቅ ከረር ባለ ድምፅ አስረድተዋል፡፡
መንግስት በሚሊዮን የሚቆጠር ዓመታዊ በጀት የበጀተለትን ይህንን ተቋም በኃላፊነት እንዲያስተዳድሩ በዶ/ር ክንፈ አብርሃ ህልፈት
ማግስት የተሾሙት አቦይ ስብሃት፣ ለቋሚ ኮሚቴው ባቀረቡት ሪፖርት ላይ፡- ‹‹ኢንስቲትዩቱ በአዋጅ የተቀመጠለትን ዓላማ ከማስፈፀም
አኳያ ቀደም ሲልም አልነበረም፤ አሁንም የለም›› ማለታቸው የሚያመላክተው የስርዓቱን ዝቅጠት ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም በአንድ
ፓርቲና በተመሳሳይ ርዕዮተ-ዓለም የሚመሩት መንግስታዊ ተቋማትም እንኳ እርስ በእርስ ተግባብተው መስራት ከማይችሉበት ደረጃ ላይ
መድረሳቸውንም ጭምር ነው፡፡
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ 

No comments: