Thursday, November 21, 2013

ለሕዝቡ ግደ የለሹ የኢህአዲግ መንግስት መወገድ አለበት( ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ)

November 21/2013
ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ

 ሰሞኑንን በሳዑዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን እየደረሰ ያለው ግፍና በደል የብዙዎቻችን ኢትዮጵያኖች አይምሮ የጓዳ እና ያሳዘነ ነገር ነው እርግጠኛ ነኝ ማንም ኢትዮጵያዊ ዜጋ በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን  መከራ በቸልተኝነት እንደማይመለከተው ምክንያቱም እየሆነ ያለው ነገር ኢትዮጵያዊ ክብርን የሚነካ እና አንገትን የሚያስደፋ ነገር ነው :: ወንድሞቻችን ተገርፈዋል ተደብድበዋል እንደ እንስሳ በአደባባይ ተቀጥቅጠዋል  የኢትዮጵያዊነትን ክብር የሆነውን ባንዲራ እንደያዙ በአደባባይ ተገለዋል ሴት እሕቶቻችንም ሳይቀሩ እንደዚሁ ዘግናኝ እና አሳፋሪ የሆነ በደል እየደረሰባቸው ነው:: እህቶቻችን በጨካኝ እና በአረመኔ የሳውዲ ጎረምሶች እና ፖሊሶች ተደብድበዋል ክብራቸው ተዋርዶል ተደፍረዋል ይህ ሁሉ በወገኖቻችን እየደረሰው ያለው ነገር ወደ ህዝብ ጆሮ ከደረሰበት ጊዚ ጀምሮ የመላው ኢትዮጵያንን ቁጣ በሀይል እና በንዴት የቀሰቀሰ ሲሆን ከየስፍራው እነዚህ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ሰይጣናዊ እና አረመናዊ ድርጊት እንዲቆም የኢትዮጵያኖ ጩኽት ከዳር እስከ ዳር በየሀገሩ እንደቀጠለ ይገኛል::ማንም ኢትዮጵያዊ የትኛውም ብሔር ቤሆን በወገኖቻችን ላይ የደረሰው በደል ያላሳዘነው ያላስቆጨው እና በህልኽ ያልቀሰቀሰው ያለ አይመስለኝም ኢትዮጵያን እና የኢትዮጵያን ዜጓች እንደ ወንድም እና እህቶቻቸው የሚያዩ ኤርትራውያን ወገኖቻችን ሳይቀሩ ይህን በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ እና በደል በአደባባይ በመውጣት እያወገዙ ይገኛሉ:: 

ዜጕች ሀገራቸውን ጥለው ከሀገር እየወጡ ለስደት እና ለመከራ የሚዳረጉበት ምክንያት ብልሹ የሆነው የወያኔ የኢህአዲግ መንግስት አስተዳደር እንደሆነ በሁሉም ዘንድ የታመነበት ሀቅ ነው:: በሳውዲም ለወንዶች እና ለሴቶች እህቶቻን መሰቃየት፣ መሞት እና ማለቅ  ቁጥር አንድ ተጠያቄው ይሄው አገሪቷን እየመራው ነው ብሎ የሚናገረው ለሃያ ሁለት አመታት በስልጣን ወንበር ላይ ቁጭ ብሎ ለኢትዮጵያ ህዝብ አንዳችም ሊፈይድ ያልቻለው በምትኩ ግን ህዝብን ለስደት  እና ለሞት የዳረገው ይኼው የወያኔ መንግስት እንደሆነ በብዙዎች ዘንድ እየተነገረ ይገኛል:: በርግጥም ሰሞኑን በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለው መከራ ለመላው ኢትዮጵያውያን ሕዝቦች የኢህአዲግን መንግስት እንኮን ሳይቀር እየደገፉ ላሉ ወገኖቻችን የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ምን ያክል የኢትዮጵያን ሕዝብ ጥቅም ለማሰከበር ያልቆመ እና  ለሚመራው እና ተወክዪለታለው ለሚለው ሕዝብ ግድ የሌለው እንደሆነ በተግባር በአደባባይ እያሰመሰከረ ይገኛል ::

በሳውዲ የሚገኙ ዜጐቻችን   የወገን እና የሀገርን እርዳታን በሚሹበት በአሁኑ ሰአት የወገን እና የሀገር ህልውና እየተረገጠበት ባለበት ሰአት የኢህአዲግ መንግሰት ግን ጆሮ ዳባ ልበስ በማለት ለህዝባቸን ምንም ያክል እርዳታን አለማድረጉ በብዙዎች ዘንድ በርግጥ ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስት አለ ወይ እያስባለ ነው የሚገኛው ::   ይህም ብቻ አይደለም በሳውዲ እየተፈፀመ ያለውን በደል በመቃወም በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን በማሰማት ላይ በሚገኙበት በአሁኑ ሰአት ሰአት በሀገር ቤት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ግን በገዛ ሀገራቸው በዜጐቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ለመቃወም አልታደሉም :: በርግጥም እራሱን ትዝብት ላይ የሚጥለውን ተግባር በመፈጸም ድምጻቸውን ለማሰማት የወጡትን ዜጐች በመደብደብ በመግረፍ እና በማሰር ከሳውዲ አረቢያ መንግሥት ጐን በመቆም ዋና ተባባሪ መሆኑን  አስመስክሯል  አልፏል:: ይህ ሁሉ ሲሆን በራሱ በወያኔ ደገፊዎች ሳይቀር የወያኔ መንግስት እየተወገዘ እና እየተብጠለጠለ ይገኛል ምክንያቱም ነገሩ የፖለቲካ ነገር ጥያቄውም የፖለቲካ ጥያቄ እንዳልሆነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በሚገባ ጠነቅቆ ያውቀዋል እና:: በሳውድ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው በደል በጣም ያላስቋጨው እና ያላንገበገበው ኢትዮጵያዊ የለም አንድ የወያኔ የኢህአዲግ መንግስት እንደሆነች በሚገባ የማውቃት ከሀገር ውጭ የምትኖሩር በዜጓቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ የሳዘናት እና የመንግስት ግድ የለሽነት ያናደዳት ወጣት አትንኩብኝ እያለች በፊስ ቡክገጽ ሳይቀር ስትክበው የነበረችውን መንግስት በመቃውም በፊስ ቡከ ገጾ ላይ እንዲህ አለች የኢትዮጵያ መንግስት ሆድ እንጅ ጭንቅላት የለውም :: እውነቷን ነው ይህች ወጣት እህታችን  ለሆድ ሳይሆን በሚገባ ህዝቡን ለመመራት እና ለማስተዳደር የተቀመጠ መንግስት ቢሆን ኖሮ በሳውዲ በዜጐቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ስቃይ ግድ ብሎት የወገን አጋርነቱን ያሳይ ነበር ይህንን ግን የወያኔ መንግስት ሊያደርገው አልቻለም::ስለዚህም ለዜጕቹ ግድ የሌለው መንግስት ለህዝብ ጥቅም የቍመ መንግስት ስለሆነ መወገድ አለበት ::
         
     አምላክ በስቃይ ውስጥ ያሉትን ወገኖች ይጠብቃቸው

No comments: