Thursday, November 21, 2013

ኢህአዴግ ስለምን ይጮኻል? (ተመስገን ደሳለኝ)

November 21/2013

በረዥሙ የኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ታሪክ , በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳ አንድም ድርሳን ፈልጎ ማግኘት የሚቻል አይመስለኝም . ሁሉም መንግስታት የተወገዱት በአመፅ አሊያም በተፈጥሮ ሞት ነውና . በ 1983 ዓ . ም ወርሃ ግንቦት በጠብ - መንጃ ኃይል ሥልጣን የተቆናጠጠው ኢህአዴግ - መራሹ መንግስትም ቢሆን , በቀድሞዎቹ ገዥዎች < የብረት ጫማ > ውስጥ ተከልሎና ተደላድሎ ዕለተ - ስንብቱን በመጠባበቅ ላይ ያለ ይመስለኛል . ዕለተ - ስንብቱ መቃረቡን የሚጠቁመው ደግሞ ከቅርብ በረዥሙ የኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ታሪክ , በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳ በረዥሙ የኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ታሪክ , በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳበረዥሙ የኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ታሪክ , በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳ አንድም ድርሳን ፈልጎ ማግኘት የሚቻል አይመስለኝም .

ሁሉም መንግስታት የተወገዱት በአመፅ አሊያም

በተፈጥሮ ሞት ነውና . በ 1983 ዓ . ም ወርሃ ግንቦት በጠብ - መንጃ ኃይል ሥልጣን የተቆናጠጠው ኢህአዴግ -
መራሹ መንግስትም ቢሆን , በቀድሞዎቹ ገዥዎች < የብረት ጫማ > ውስጥ ተከልሎና ተደላድሎ ዕለተ - ስንብቱን
በመጠባበቅ ላይ ያለ ይመስለኛል . ዕለተ - ስንብቱ መቃረቡን የሚጠቁመው ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ልክ
እንደ ደርግ የመጨረሻዎቹ ወራት ሁሉ , ግንባሩና አጋር ፓርቲዎቹ ለየት ባለ መልኩ በራሳቸውና
በሹማምንቶቻቸው ላይ በአደባባይ የተቃውሞ ድምፅ ማሰማት መጀመራቸው ነው . የዚህ ፅሁፍ ተጠየቅም
ይህ ነውና ተጨባጭ እውነታውን ለማብራራት በቂ የሆኑ አስረጂዎችን በአዲስ መስመር በዝርዝር ለመመልከት እሞክራለሁ .

ስረጅ አንድ

በ 2005 ዓ . ም መጨረሻ ላይ የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ዓመታዊ ሪፖርቱን ለሕዝብ ተወካዮች ባቀረበበት ወቅት ከአገዛዙ የተለየ
ድምፅ የተሰማው እንደ ወትሮው ሁሉ , በም / ቤቱ ተቃዋሚ ፓርቲን ከወከለው < አንድ ለእናቱ > አቶ ግርማ ሰይፉ ብቻ አይደለም ;
ኢህአዴግ በአምሳሉ ከፈጠራቸው አጋር ፓርቲዎችም ጭምር እንጂ .

በዕለቱ ሚንስትሩ ዶ / ር ሽፈራው ተክለማርያም በመንግስት በመገንባት ላይ ያለውን የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካን አስመልክቶ < አክራሪ >
ካላቸው መነኮሳትና < ጥቂት > መዕምናን < ግርግር የመፍጠር ሙከራ > ባለፈ የተከሰተ የጎላ ችግር አለመኖሩን በሪፖርቱ መጥቀሱን ተከትሎ

የአፋር ክልል ተወካዩ በአጋርነት ያነበረውን ስርዓት እንዲህ ሲል ነበር የተቸው -

<< ለፋብሪካው ግንባታ ተብሎ ከአካባቢው የተፈናቀሉ ነዋሪዎች እንዲሰፍሩ የተደረገበት ቦታ ውሃና መብራት ያሌለው ነው ; ይህ ለምን
ሆነ ? ብለን ስንጠይቅ < ድሮም የነበሩበት ቦታ መብራትና ውሃ የለውም > በማለት ይመልሱልናል . በአጠቃላይ በአፋርና አካባቢው
በሪፖርቱ ያልተካተቱ ብዙ ችግሮች አሉ . >>

የሶማሌ ክልል ተወካይም በበኩሉ በዚሁ ዕለት የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር < የሰብዓዊ መብት አያያዝ > ን በተመለከተ አድበስብሶ ማለፉን

የተቃወመው በሚከተለው አኳኋን ነበር -

<< በእኛ አካባቢ የሰብዓዊ መብት አይከበርም ; ሰዎች ይገደላሉ ; ይታሰራሉ ; ይደበደባሉ . >> ( በርግጥ በመልከዓ ምድር ለአካባቢው
ከማንም በላይ የሚቀርበው የሀረሪው ተወካይ ብዙውን ጊዜ በምክር ቤቱ ስለማይገኝ በዕለቱ በቀረበው ሪፖርት ላይ ቅሬታ ይኑረው ድጋፍ
ማወቅ አልተቻለም )

አስረጅ ሁለት

ጥቅምት 22 ቀን 2006 ዓ . ም የኢትዮጵያ የሰላምና ልማት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር አቦይ ስብሃት ነጋ , በህዝብ ተወካዮች ም / ቤት
ለውጭ , መከላከያና ደህንነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ , የዓመቱን በጀት ለማፀደቅ ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት , ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
መ / ቤት ጋር ተግባብተው መስራት አለመቻላቸውን በግልፅ ተናግረዋል . ኢንስቲትዩቱ የተመሰረተበት አቢይ ዓላማ << የውጭ ጉዳይ
ፖሊሲ በሚያስገኘው ውጤት ዙሪያ ጥልቅ ጥናት ለማካሄድ >> መሆኑ ቢታወቅም , ውጭ ጉዳይ << ይህንን አጥኑልን >> ብሎም ሆነ አቅጣጫ

አሳይቶ እንደማያውቅ ከረር ባለ ድምፅ አስረድተዋል .

መንግስት በሚሊዮን የሚቆጠር ዓመታዊ በጀት የበጀተለትን ይህንን ተቋም በኃላፊነት እንዲያስተዳድሩ በዶ / ር ክንፈ አብርሃ ህልፈት
ማግስት የተሾሙት አቦይ ስብሃት , ለቋሚ ኮሚቴው ባቀረቡት ሪፖርት ላይ - << ኢንስቲትዩቱ በአዋጅ የተቀመጠለትን ዓላማ ከማስፈፀም
አኳያ ቀደም ሲልም አልነበረም ; አሁንም የለም >> ማለታቸው የሚያመላክተው የስርዓቱን ዝቅጠት ብቻ አይደለም ; ይልቁንም በአንድ
ፓርቲና በተመሳሳይ ርዕዮተ - ዓለም የሚመሩት መንግስታዊ ተቋማትም እንኳ እርስ በእርስ ተግባብተው መስራት ከማይችሉበት ደረጃ ላይ
መድረሳቸውንም ጭምር ነው .

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

No comments: