Monday, November 11, 2013

በሳኡዲ አረቢያ የሚፈጸመው ግድያ እና የኢትዮጵያ መንግስት ሴራ

November 11/2013

 ባሳለፍነው ወር ውስጥ የኢትዮጵያ መንግስት በሳኡዲ አረቢያ የሚጓዙ ስደተኞችን አግደናል ሲል ለመገናኛ ብዙሃኖች መጠቆሙ የሚታውስ ሲሆን ያንን ተከትሎም ሆነ ከዚህ ቀደም ይደረጉ የነበሩ አንዳንድ ሁኔታዎችን ተመልክቶ አንዳንድ ምልከታዎችን ለመጠቆም ወደድን ።

የኢትዮጵያ መንግስት በሃገር ውስጥ የሚገኙትን ለኡምራ ጉዞ በሚል ፈቃድ በማግኘት እስከ አረብ አገራት ድረስ በመደለል ስራ እናስገባቿለን በማለት ሴት እህቶቻችንን እና ወንድሞቻችንን ጉዞአቸውን ወደዚያው እንዲያመሩ አቅጣጫቸውን እየቀየሩ ህብረተሰቦችን ወደ አልተፈለገ ጉዳት ውስጥ ሲጥሉአቸው እንደነበር በተለያዩ ጊዜያቶች ይነገሩ የነበሩ የረጂም ጊዜ ታሪኮች ናቸው ።ይባስ ብሎ እነዚህ ደላላዎች በሃገር ውስጥ ተቀምጠው ከአሰሪዎቻቸው ጋር በመነጋገር ገንዘብ ወደ ደላላዎቻቸው ብቻ እንዲላክ እንጂ ለሰራተኞቹ በእጃቸው እንዳይደርሳቸው በማድረግ የብዙሃኑን የድሃ ቤተሰብ ልጆች ደም ሲነጥቁ መክረማቸውም ሌላኛው ግልጽ ዘረፋ የተካኑት ግለሰቦች መሆናቸውን ማንም ሰው የሚረዳው ጉዳይ ነበር ።ሆኖም እንዲህ አይነቱ ክስተት ተፈጠረ ሲባል እኛ አናውቅም አሰሪዎቻቸውንም ሆነ በአረብ አገራት የሚገኙትን ደላላዎች አናውቅም በማለት የብዙዎችን ደም ደመ ከልብ ያደረጉት እነዚሁ የግል አስጎብኝ ድርጅት ኖሮአቸው ዜጎቻቸውን በህገወጥ እና በቀላሉ ልጥቅም ብለው በአረብ አገራት ላሉት ባለሃብቶች የሸጡአቸው ዜጎች መሆናቸውን ሳልገልጽ አላልፍም ።ለዚህም ሁሉ ጥፋት ተጠያቂ እነዚህም ወገኖች በህገ ወጥ ስራቸው ብቻ ሊጠየቁበት የሚገባው ዋነኛው ጉዳይ ሆኖ ሊታይ ይገባዋል ።
ከዚህም ባሻገር ለዘመናት እንዲህ ዜጎቻችንን ለርካሽ ባርነት የላኳቸውን ወገኖች ዘወር ብለው ያላዩአቸውን እንዚህን ደላላ ተብዬዎች ከባለፉት ሁለት አመታት ጀምሮ መንግስት እና እንዲሁም ጥቂት የመንግስት ደጋፊ የሆኑ ባለስልጣናት ደጋፊ የሆኑ ሰዎች ይህንን ስራ በህጋዊ መልኩ አድርገን እንሰራለን በማለት በወር ወደ 45.000 የሚጠጉ የቤት ሰራተኞችን እንልካለን በማለት ከባለሃብቱ ሼክ መሃመድ አላህሙዲ ጋር የሚሰራ አንድ ትልቅ የጉዞ አስጎብኝ ወኪል በመፍጠር ለሳኡዲ መንግስት ሴትም ሆነ ወንድ ሰራተኞችን ሊያቀርቡ እንደሚችሉ መፈራረማቸውን በይፋ መግለጻቸውን እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህገ ወጥ የሚሰሩትን ድርጅቶች ቀስ በቀስ እያመነመኑ እንዲዘጉ ማድረጋቸው የሚታወቅ ሲሆን ..ለህዝባችን በተወሰነ መልኩ እፎይታን ቢሰጥም በእጅ አዙር እራሳቸው ስራውን ሊሰሩት ማሰባቸውን እና ሃሳቡን መቀልበሳቸው በሰፊው የተጋለጠባቸው ግን አሁን መሆኑን ሁሉም ሰው  ተረድቶታል ።መንግስት በህጋዊ መንገድ አቀርባቸዋለሁ ያላቸውን ሰራተኞች እራሱ ጉዳዩን ፈጽሞ እራሱ ልኮ ጠበቃ ነኝ ብሎ በሳኡዲ አረቢያ የሚገኘው ቆንጽላ በጥቃታቸው ጊዜ ጉዳታቸውን እንዲሰማላቸው አደርጋለሁ ሲልም መናገሩ አይዘነጋም ።
ዛሬ ደግሞ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ  በቃል አቀባይነታቸው መሰረት
በሳዑዲ በመከራና ስቃይ ውስጥ ያሉ ወገኖቻችንን አስመልክቶ የመንግስት ቃል አቀባይ  የተባሉት የቁጭ በሉ ሰው ዲና ሙፍቲ ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ፦”እየተባረሩ ያሉት ህጋዊ ያልሆኑት ናቸው” ብለዋል ተናግረዋል ።ዲና  በሌላም በኩል  ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ ፖሊሶች ስለመገደላቸው የተረጋገጠ ማስረጃ እንደሌላቸው አስረግጠው ገልጸዋል  ሆኖም የሃገሪቱ መንግስት በመገናኛ ብዙሃኑ የተገደሉትን ዜጎች እያሳየ መዋሉን ሲ ኤን ሲ የተባለው የቻይና ቴሌቪዥን ሲያሳይ ቆይቶአል ። ሆኖም የ ዲና ሙፍቲ አነጋገር የሁሉንም ቀልብ ስቦአል ምክንያቱም የሃገሪቱ ተወካይ ሳይሆኑ የሳኡዲ ቃል አቀባይ መስለው መታየታቸው ነው ።
የዲና ሙፍቲ ጉዳይ ወደ ኋላ ተወት እናድርገው እና አቶ ቴዎድሮስ አድሃኖም በሰሞኑ በተጠመዱበት ቲዊተር ስለ ህዝቦቻቸው ሲናግሩ ከአረብ መንግስታቶች ጋር በመምከር ላይ እንዳሉ እና መፍትሄ ሊያመጡ እንደሚችሉ ገልጸዋል ።በትላንትናው እለትም በመንግስት ሃይሎች የሚመራው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም እንደዚሁ ጅብ ከሄደ ጩኸቱን አስምቶአል ።
ከ16500 በላይ ኢትዮያውያኖች በመካ አቅራቢያ ፣በየመን ዳር ድንበር እና እንዲሁም በሳኡዲ አረቢያ ከተማ በሚገኙ እስርቤት ውስጥ ተጉዘው በእስር ስቃይ ላይ እየማቀቁ ይገኛል ።እንደ ሃገሪቱ ናሽናል ቴሌቪዥን ዘገባ ከሆነ እያንዳንዱ እስረኛ ከ500 እስከ 1000 የአሜሪካን ዶላር የሚደርስ ቅጣት ይጠብቀዋል ይህንን የማይፈጽም ከሆነ ደግሞ እስሩን ጨርሶ ሊፈታ እንደሚችል እና ዳግመኛ ወደዚያች ምድር እንዳይመጣ በሚያደርግ የአሻራ ፊርማ አስወጥተው ሊያባርሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል ። ታዲያ ይህ ሁሉ እየሆነ ያለው ከኢትዮጵያ መንግስት በተሰጠን  ትእዛዝ ነው ብለው ተናግረዋል የሚሉ መረጃዎች ከወደ ሳኡዲ እየተሰማ ይገኛል ፣ሆኖም ግን ይህ ምን ያህል እውነታ እንደሆነ ማረጋገጫው ባይኖረኝም ይህንን የጻፈውን ብሎግ ግን ማቅረብ መቻሌን ውሸታም አያሰኘኝም ስለዚህ ሙሉውን እንዲህ ይነበባል
ከዚህ ቀጥሎ ከክሊክ ሃበሻ የተዘገበውን ዜና አንዲህ ተቀናብሮ የተቀመጠ ሲሆን እኔም በዚህ መልኩ  ጽሁፉን አስቀምጠው እና ከዚያም ሊንኩን አያይዤ ለማስቀመጥ እሞክራለሁ ። “ቴዎድሮስ አድሃኖም ህገወጥ ኢትዮጵያውያን እንዲያዙ የተስማማበት ሰነድ አለን”የሳኡዲ ባለስልጣናት
 | 10 בNovember 2013 | 0 Comments
በሪያድ የዛረው ሰልፍየሚመጣውን አደጋ በመፍራትተበትኗል::
999410_10201428110199302_1866404023_n“ቴዎድሮስ አድሃኖም ህገወጥኢትዮጵያውያን እንዲያዙየተስማማበት ሰነድአለን”የሳኡዲ ባለስልጣናት
አምስተኛ ቀኑን የያዘው የሳኡዲጸረ ኢትዮጵያውያን ዘመቻእንደቀጠለ ሲሆን ሁኔታዎችንለመፍታት የተደረጉ ጥረቶችከዚህ
ቀደም የኢትዮጵያመንግስት እና የቆንስላውዲፕሎማቶች በሰርኡት ስህተትመስመር ሊይዝ አልፈለገም::
እንደ ሳኡዲ ባለስልጣናትአነጋገው የውጪ ጉዳይሚኒስትሩ ከዚህ ቀደም ባደረጉት ጉብኝት ሃገራቸው ህገወጥ ኢትዮጵያውያንን እንዲያስወጣ እና በምትኩ40,000 ህጋዊ ስደተኞችን እንደሚልኩ የፈረሙበትን ማስረጃ ይዘዋል::
በሪያድ መንፉሃ ወደ ሃገራችን ስደዱን በሚል መንፉሃ ባንክ አልራጅህ አካባቢ በርካታ ኢትዮጵያውያን መንግስትየወሰደውን እርምጃ ተቃውመው ሰልፍ መውጣታቸው ተሰማ። እንደ አረብ ኒውስ ዘገባ መሰረት በሰልፈኞችበተወረወሩ ድንጋዮች አንድ የሳውዲ ዜጋ መሞቱንም ዘግቧል።
እነዚሁ በነዋሪዎች ድብደባና በደል የደረሰባቸው ኢትዮጲያውያን ወደ ሪያድ ኢምባሲና ኮሚኒቱ መስሪያ ቤትበእግራቸው ያመሩ ሲሆን መንፉሃ አካባቢ የቀሩት ከፖሊስ ጋር ባደረጉት ግጭት አንድ የፖሊስ መኪናእንደተሰበረ የአይን እማኞች ገልጸውልኛል።http://www.clickhabesh.com/?p=103630
ታዲያ እንዲህ ከሆነማ ሴራውን የጠነሰሱት የራሳችን ወገኖች ከሆኑ ለዚህም ተጠያቂው እራሳቸው ስለሆኑ ፣በወጥመድ ውስጥ እራሳቸውን አሾልከው ላለማስገባት ባደረጉት ጥረት ሸፋፍነው ማለፍን ስለፈለጉ የህዝባቸውን ሰቆቃ እያዩ ዝም ማለትን መርጠዋል ፡፤ይህንንም ሰቆቃ እና ግፍ ግድያ እንዲሁም የሴቶችንም ሆነ የወንዶችን አስገድዶ መደፈር እንዲመጣ ያደረጉት እንዚሁ ጨካኝ የሆኑ ገዢ መደቦቻችን ናቸው ማለት ነው። በነገራችን ላይ በመካ መዲና አካባቢ የተወሰዱት እስረኞች በሙሉ ፣የታሰሩት ወገኖች በግብረ ሰዶማውያን በታሰሩበት እስርቤት እንደሆነ ለመጠቆም እወዳለሁ ።
ይህ ቦታ ከፍተኛ ሙቀት ያለው አካባቢ ከመሆኑ የተነሳ የሰው ልጆችን ለመቅጣት ሆን ተብሎ የተዘጋጀ እና ማኛውም ሰው በተፋፈነ ክፍል ውስጥ አይደለም ለቀናት ለሰአታት መቀመጥ የማይችልበት እስርቤት ሲሆን ከዚህም ባሻገር የሚጠጣው ዉሃ ከፍተና ጨዋማ የሆነ ከመሆኑም በላይ ስውነትን ለመላላጥ እና ለተለያዩ ጉዳቶች ሊያደርስ የሚችል መሆኑን ያገኘኋቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ ።ይኅንን ስቃይ እና መከራ ለምን ዜጎቻቸው እንዲጋፈጡት ፈለጉ ፣መንግስት እንዲህ አይነቱን የክፋት ወንጀል ለምን በህዝቦቹ ላይ መፈጸም አስፈለገው ፣ለምንስ በስደት ያሉት ወገኖች ላይ አነጣጠረ የሚለው ምላሽ ።
ዋነኛው ምክንያት በህገወጥ ገቡ የተባሉት ወገኖች በሳኡዲ አረቢያ የሚገኘውን ክፍት የስራ ቦታ ስለሚሸፍኑት መንግስት በህጋዊ መንገድ አቅርባቸዋለሁ ያላቸው ሌሎች ዜጎቹን ስራ አጥተው እንዳይሰቃዩበት ስጋት ስለያዘው እና ፣አዲስ የሚጀምረው የጉዞ ሂደት እንዳይደናቀፍበት ቅድመ ጥንቃቄ ለመውሰድ ያስችለው ዘንድ ህጋዊ አልሆኑም ያላቸውን ህዝቦቹን በግዳጅ ከሳኡዲ መንግስት ጋር በመተባበር እንዲያስወጡ መምከሩ ግድ ሆኖ ስለታየው ያንን ሃላፊነት እራሱ ላይ መሸከምን ችሎአል ።ለዚህ ሲባል የሳኡዲ መንግስት በንጹሃን ህዝቦች ላይ ጥቃትን ፈጽሞአል መንግስትም ይህንን አላየሁም ሲል ድፍን አድርጎ የገለጸ ሲሆን በትላንትናው እለት በቴሌቪዝን የአየር ሰአት ላይ ለማረጋገጥ እንጥራለን ሲል ቃሉን ሲያጥፍ ተሰምቶአል ።
እንደ ማጠቃለያ ...መፍትሄው በሃገር ውስጥም ሆነ ተለያዩ አገራት የምንገኝ ዜጎች የህዝቦቻችንን መብት ለማስከበር በምናደርገው ጥረት ማናችንም በአለን ሃይል ተጠናክረን በመምጣት የህዝቦቻችንን መብት ማስከበሩን ግፊት በማድረግ በአረቡ አለም ላይ ጫና እንዲደረግ መጠየቅ እና መምከር ያስፈልገናል ከዚያም ባሻገር በሳኡዲ አረቢያ ኢምባሲ ቅርንጫፍ ቢሮዎችም ሆነ ቆንጽል ስህፈት ቤቶች በመገኘት ድምጻችንን እናሰማለን ከዚያም ቀጥሎ የዚህን አድሃሪ የሆነ መንግስት ሴራ ማጋለጡም ቢሆን ለጉዳት የሚዳርገን አይመስለኝም እና ሁላችንም ለህዝቦቻችን ቅድሚያ በመስጠት የንጹሃኖችን ህይወት እናትርፍ እያልኩኝ እለያችኋለሁ ።ስለያችሁ በአሜሪካ የሚገኙትን ሴናተሮች እና አገረ ገዢዎችን ኢሜል አድራሻ አያይዤ ሳቅርብላችሁ ሁላችሁም ጩኸታችሁን በኢሜሎቻቸው ላይ ያድርሱአቸው የሚለው የመጨረሻው የልመና ቃሌ ነው ሰላም ያገናኘን ።ዘላለም ገብሬ ከማለዳ ታይምስ መረጃ ማእከል ።
John_McCain@McCain.senate.gov,senator@akaka.senate.gov,senator@biden.senate.govsenator_bingaman@bingaman.senate.gov,senator@breaux.senate.govsenator_byrd@byrd.senate.gov,senator_carnahan@carnahan.senate.govsenator@clinton.senate.gov,senator@conrad.senate.govsenator@dodd.senate.govsenator@dorgan.senate.gov,dick@durbin.senate.govrussell_feingold@feingold.senate.gov,senator@feinstein.senate.govbob_graham@graham.senate.gov,tom_harkin@harkin.senate.govvermont@jeffords.senate.govtim@johnson.senate.gov,senator@kennedy.senate.govjohn_kerry@kerry.senate.gov,senator_kohl@kohl.senate.govsenator_leahy@leahy.senate.gov,senator@levin.senate.govblanche_lincoln@lincoln.senate.gov,senator@mikulski.senate.govsenator_murray@murray.senate.gov,senator@billnelson.senate.gov, jack@reed.senate.govsenator@rockefeller.senate.gov,senator@schumer.senate.govsenator@stabenow.senate.gov,senator_torricelli@torricelli.senate.gov

No comments: