![](https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhHEsvdQWzxccuqRFfiMZOdZgT5qlLCij5yl3EC433F_sAjfTu4zqWsurVkLKvtbzWJMcsfwxkHJqqkbHntyAscUxzZ8plXXFVQBlqmWbETtNTG8EG5zkI3ZsiEGO3RssFXA5x9Ifu5gvM/s1600/safe_image%5B2%5D.png)
የጸጥታ ኃይሎቹ በሚያካሂዱት ፍተሻ ባህርዳርና አካባቢዋ ዉስጥ የመንግስትና የግሉ ዘርፍ ስራና ህዝባዊ እንቅስቃሴዎች የተስተጓጓሉ ሲሆን ህዝቡም በከፍተኛ ደረጃ እየተንገላታ መሆኑን የከተማዋ ነዋሪዎች በመናገር ላይ ይገኛሉ። የወያኔ አገዛዝ በህዝብ ላይ ለመፈጸም ለማያስባቸዉ ጭፍጨፋዎች ህጋዊ ሽፋን ለመስጠት እንዲህ አይነት እርምጃ መዉሰዱ የተለመደ ነዉ ያሉት አንድ ስማቸዉ እንዲገለጽ ያልፈለጉ ከፍተኛ የኢህአዴግ ባለስልጣን ይስ የሰሞኑ የባህርዳር ፍተሻ ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ አገዛዙን በማስጨነቅ ላይ ያለዉን የወጣቶች እንቅስቃሴ ለማፈንና አባላቱን ለመግደል የታቀደ እንደሆነ ገልጸዋል። ዊኪሊክስ የተባለዉ ሚስጢር አጋላጭ ድርጅት የዛሬ ሁለት አመት ይፋ ያደረገው መረጃ በግልጽ እንዳሳየዉ የአሜሪካ ኢምባሲ የኢትዮጵያ መንግስት በአገሪቱ የሽብር አደጋ አለ ለማስባል ሆን ብሎ ፍንዳታዎችን ያቀናብራል ብሎ እንደሚያምን መግለጹ ይታወሳል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በባህርዳር አንድ የባጃጅ ሹፌር በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድሎ ተገኝቷል። በወጣትነት እድሜ ክልል የሚገኘዉና የቀበሌ 7 ነዋሪ የሆነው ይህ ወጣት በከፍተኛ ሁኔታ የተደበደበ ከመሆኑም በላይ ሁለት አይኖቹ በአሳቃቂ ሁኔታ ወጥተዉ ከተጣለበት ቦታ ከሁለት ቀ አይኖቹ ወጥተው ከቀናት በሁዋን በኋላ ነው በፍለጋ የተገኘዉ። ኢሳት ሬድዮና ቴሌቪዥን በግድያዉ ዙሪያ የባሀርዳርን ፖሊስ ኮሚሽን ለማናገር ያደረገዉ ሙከራ እንዳልተሳካ ለማወቅ ተችሏል።
No comments:
Post a Comment